From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
|
አስቴር ፡ አበበ (Aster abebe)
|
|
፩ (1)
|
ክብር ፡ የበቃህ ፡ ነህ (Keber Yebeqah Neh)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፳ ፻ ፱ (2017)
|
ቁጥር (Track):
|
፬ (4)
|
ርዝመት (Len.):
|
4:00
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የአስቴር ፡ አበበ ፡ አልበሞች (Albums by Aster abebe)
|
|
እስኪ ፡ ይንገረኝ ፡ ሚያውቅ ፡ ካለ ፡ ስለእርሱ ፡ ጅማሬ
እስኪ ፡ ይንገረኝ ፡ ሚያውቅ ፡ ካለ ፡ ስለእርሱ ፡ ፍጻሜ
እስኪ ፡ ይንገረኝ ፡ ሚያውቅ ፡ ካለ ፡ ስለአካሄዱ
እስኪ ፡ ይንገረኝ ፡ ሚያውቅ ፡ ካለ ፡ የአምላኬ ፡ መንገዱን (፪x)
ምን ፡ ማወራው ፡ አለኝ ፡ ካነበብኩት ፡ በቀር
ከፍቅሩ ፡ በቀር ፡ ከምክሩ/ከነገሩኝ ፡ በቀር
እንዴት ፡ እንደወጣሁ ፡ ያንን ፡ ክፉ ፡ ሰፈር/መንደር
የማውቀው ፡ ይሄን ፡ ነው ፡ ስለጌታ ፡ ነገር (፪x)
የተማረ ፡ ሰው ፡ ብዙ ፡ የተተወለት
መተላለፉ ፡ ኃጢአቱ ፡ የተረሳችለት
አንተን ፡ ቢያመሰግንህ ፡ ቢልስ ፡ ጐንበስ ፡ ቀና
አሳነሰብህ ፡ እንጂ ፡ መቼ ፡ ይበዛና (፪x)
የበዛውን ፡ የአንተን ፡ ምሕረት ፡ አይቼ
የተትረፈረፈውን ፡ ፀጋህን ፡ ቀምሼ
አንተን ፡ አለማምለክ ፡ ነውር ፡ ሆኖ ፡ ታየኝ
ይልቅስ ፡ መጨመር ፡ መቀኘትን ፡ አሰኘኝ
ላመስግንህ (አሃ) ፡ ከፍ ፡ ላድርግህ (አሃ) ፡ ልቀኝልህ (አሃ) ፡ ልዘምርልህ
የርህራሄ ፡ አምላክ ፡ ነህ ፡ ዓይኖቼ ፡ አይተውሃል
ከትላንቱ ፡ ይልቅ ፡ ልቀርብህ ፡ ገዶኛል (፪x)
ምን ፡ ማወራው ፡ አለኝ ፡ ካነበብኩት ፡ በቀር
ከፍቅሩ ፡ በቀር ፡ ከምክሩ/ከነገሩኝ ፡ በቀር
እንዴት ፡ እንደወጣሁ ፡ ያንን ፡ ክፉ ፡ ሰፈር/መንደር
የማውቀው ፡ ይሄን ፡ ነው ፡ ስለጌታ ፡ ነገር (፪x)
|