እስቲ ፡ ይንገረኝ (Esti Yengeregn) - አስቴር ፡ አበበ

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
አስቴር ፡ አበበ
(Aster abebe)

Lyrics.jpg


(1)

ክብር ፡ የበቃህ ፡ ነህ
(Keber Yebeqah Neh)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፱ (2017)
ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 4:00
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአስቴር ፡ አበበ ፡ አልበሞች
(Albums by Aster abebe)

እስኪ ፡ ይንገረኝ ፡ ሚያውቅ ፡ ካለ ፡ ስለእርሱ ፡ ጅማሬ
እስኪ ፡ ይንገረኝ ፡ ሚያውቅ ፡ ካለ ፡ ስለእርሱ ፡ ፍጻሜ
እስኪ ፡ ይንገረኝ ፡ ሚያውቅ ፡ ካለ ፡ ስለአካሄዱ
እስኪ ፡ ይንገረኝ ፡ ሚያውቅ ፡ ካለ ፡ የአምላኬ ፡ መንገዱን (፪x)

ምን ፡ ማወራው ፡ አለኝ ፡ ካነበብኩት ፡ በቀር
ከፍቅሩ ፡ በቀር ፡ ከምክሩ/ከነገሩኝ ፡ በቀር
እንዴት ፡ እንደወጣሁ ፡ ያንን ፡ ክፉ ፡ ሰፈር/መንደር
የማውቀው ፡ ይሄን ፡ ነው ፡ ስለጌታ ፡ ነገር (፪x)

የተማረ ፡ ሰው ፡ ብዙ ፡ የተተወለት
መተላለፉ ፡ ኃጢአቱ ፡ የተረሳችለት
አንተን ፡ ቢያመሰግንህ ፡ ቢልስ ፡ ጐንበስ ፡ ቀና
አሳነሰብህ ፡ እንጂ ፡ መቼ ፡ ይበዛና (፪x)

የበዛውን ፡ የአንተን ፡ ምሕረት ፡ አይቼ
የተትረፈረፈውን ፡ ፀጋህን ፡ ቀምሼ
አንተን ፡ አለማምለክ ፡ ነውር ፡ ሆኖ ፡ ታየኝ
ይልቅስ ፡ መጨመር ፡ መቀኘትን ፡ አሰኘኝ

ላመስግንህ (አሃ) ፡ ከፍ ፡ ላድርግህ (አሃ) ፡ ልቀኝልህ (አሃ) ፡ ልዘምርልህ
የርህራሄ ፡ አምላክ ፡ ነህ ፡ ዓይኖቼ ፡ አይተውሃል
ከትላንቱ ፡ ይልቅ ፡ ልቀርብህ ፡ ገዶኛል (፪x)

ምን ፡ ማወራው ፡ አለኝ ፡ ካነበብኩት ፡ በቀር
ከፍቅሩ ፡ በቀር ፡ ከምክሩ/ከነገሩኝ ፡ በቀር
እንዴት ፡ እንደወጣሁ ፡ ያንን ፡ ክፉ ፡ ሰፈር/መንደር
የማውቀው ፡ ይሄን ፡ ነው ፡ ስለጌታ ፡ ነገር (፪x)