እንኳንም ፡ አገኘኸኝ (Enkwanm Agegnehegn) - አስቴር ፡ አበበ

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

እንኳንም

አስቴር ፡ አበበ
(Aster Abebe)

Aster Abebe 1.jpg


(1)

ክብር ፡ የበቃህ ፡ ነህ
(Keber Yebeqah Neh)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፱ (2017)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 4:11
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአስቴር ፡ አበበ ፡ አልበሞች
(Albums by Aster Abebe)

የራቀ ፡ ሰፈሬን ፡ ጠንክሮ ፡ የታጠረ ፡ አጥሬን
ምክንያት ፡ ፈልጎ ፡ ፈጥሮ ፡ የራሱን ፡ ሰበብ
ተቀምጦ ፡ ቆየኝ ፡ ከጉድጓዱ ፡ አጠገብ (፪x)

ሳላውቀው ፡ ማንነቱን ፡ የነፍሴን ፡ መድሃኒት
እንዲህ ፡ እንዲያ ፡ እያልኩኝ ፡ ስደረድር ፡ ምክንያት
ለጥቆ ፡ ገባና ፡ ወደ ፡ ህይወቴ ፡ ባህር
ለራሴው ፡ ነገረኝ ፡ የእራሴን ፡ ሚስጥር
የሚጠጣ ፡ ውሃ ፡ በእኔ ፡ ዘንድ ፡ ፍለጋ
መች ፡ ቆመ ፡ ከደጄ ፡ እራሱን ፡ ሊያረካ
ህይወትን ፡ ሊችረኝ ፡ ከከበቡኝ ፡ ሁሉ
አፋቶ ፡ የእራሱ ፡ አደረገኝ ፡ በፍቅሩ

መስሎኝ ፡ በምድሩ ፡ ሰላምና ፡ እርካታ
ከአንዱ ፡ ተጋብቼ ፡ አንደኛውን ፡ ስፈታ
አይቶ ፡ መባከኔን ፡ በእርግጥ ፡ አዝኖልኛል
በአፉ ፡ ቃል ፡ እፎይታ ፡ ወደ ፡ ቤቴ ፡ ገብቷል

እንኳንም ፡ አገኘኸኝ ፡ አንተ ፡ ወዳጄ
እንኳንም ፡ ቀድመኸኝ ፡ ተገኘህ ፡ ከደጄ
ቢሆንማ ፡ ሌላው
ዛሬን ፡ በአይኔ ፡ ባላየሁ

ቤተ ፡ ዘመድ ፡ ይስማ ፡ ጓደኛ ፡ ጎረቤት
ላፍታም ፡ አልዘገይም ፡ ሳልነግር ፡ ይህን ፡ እውነት
ጉዴን ፡ ለነገረኝ ፡ የኋላ ፡ ታሪኬን
ልቤ ፡ እርሱ ፡ ጋር ፡ ቀርቷል ፡ ወስዶልኝ ፡ ሸክሜን

እንኳንም ፡ አገኘኸኝ ፡ አንተ ፡ ወዳጄ
እንኳንም ፡ ቀድመኸኝ ፡ ተገኘህ ፡ ከደጄ
ቢሆንማ ፡ ሌላው
ዛሬን ፡ በአይኔ ፡ ባላየሁ (፫x)