From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
አስቴር ፡ አበበ (Aster Abebe)
|
|
፪ (2)
|
ሃሌሉያ (Hallelujah)
|
ዓ.ም. (Year):
|
"፳፪፬" is not in the list (፲ ፱ ፻ ፹ ፩, ፲ ፱ ፻ ፹ ፪, ፲ ፱ ፻ ፹ ፫, ፲ ፱ ፻ ፹ ፬, ፲ ፱ ፻ ፹ ፭, ፲ ፱ ፻ ፹ ፮, ፲ ፱ ፻ ፹ ፯, ፲ ፱ ፻ ፹ ፰, ፲ ፱ ፻ ፹ ፱, ፲ ፱ ፻ ፺ ፩, ...) of allowed values for the "ዓመተምህረት" property. (2024)
|
ቁጥር (Track):
|
፪ (2)
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የአስቴር ፡ አበበ ፡ አልበሞች (Albums by Aster Abebe)
|
|
ለሚያወራህ ፡ ውበት ፡ ለሚለብስህ ፡ ጌጥ
ሮጦ ፡ ለተጠጋህ ፡ የማምለጫ ፡ አለት
ህይወት ፡ ከሞት ፡ ወዲያ ፡ እርስቱ ፡ ላረገህ
ለአፍታ ፡ እንኩዋን ፡ የማትጎድል ፡ ለሰው ፡ ሙላቱ ፡ ነህ
አንተን ፡ ነው ፡ እንጂ
ጥብቅ ፡ አድርጎ ፡ መያዝ ፡ ያዘኝ ፡ እያሉ
ማልዶ ፡ በጠዋት
በአንተው ፡ እጅ ፡ ነቅቶ ፡ መዋል ፡ ደጅ ፡ እየጠኑ (፪x)
ዓይኔን ፡ ጉዳዬ ፡ ላይ ፡ ማድረግ
ፍለጋዬን ፡ እድሜ ፡ ልክ ፡ መፈለግ
ናፍቆቴን ፡ ሳላርፍ ፡ መናፈቅ
ጉጉቴን ፡ ሳልደክም ፡ መፈለግ
እንዲሆንልኝ ፡ ይብዛልኝ ፡ ጸጋህ
ጊዜው ፡ ደርሶ ፡ እስክደርስ ፡ አንተ ፡ ጋር
ገባ ፡ ወጣ ፡ እግሬ ፡ ሳይልብኝ ፡
ፍለጋዬ ፡ ሳትጎድል ፡ ብዛልኝ
በድነቴ ፡ ጠዋት ፡ በገባኸኝ ፡ ማግስት
ጨዋታ ፡ ወሬዬ ፡ መወደዴን ፡ ማድነቅ
ዘምሬህ ፡ አልጠግብ ፡ አውርቼህ ፡ አልረካ
ይህቺ ፡ ትንሽ ፡ ልቤ ፡ ለፍቅርህ ፡ ሸፍታ
አልደግ ፡ አንተ ፡ ላይ ፡ እራሴን ፡ አልቻል
አጓጉል ፡ ነው ፡ ሁሉም ፡ ያላንተ ፡ መች ፡ ያምራል
መጠበቂያ ፡ አጥሬ ፡ መሰንበቻዬ ፡ ነህ
ልኑር ፡ እንደፈዘዝሁ ፡ ዓይኔ ፡ አንተን ፡ እያለ
ጉዳዬ ፡ አንተው ፡ መናፈቄ ፡ መምጣትህ
ጉጉቴ ፡ ዓይኔ ፡ እስከሚያይህ
ሁሌ ፡ ሁሌ ፡ ሁሌ ፡ ሁሌ ፡ አንተን ፡ ብቻ
እስከ ፡ እድሜዬ ፡ መቋጫ (፬x)
ዓይኔን ፡ ጉዳዬ ፡ ላይ ፡ ማድረግ
ፍለጋዬን ፡ እድሜ ፡ ልክ ፡ መፈለግ
ናፍቆቴን ፡ ሳላርፍ ፡ መናፈቅ
ጉጉቴን ፡ ሳልደክም ፡ መፈለግ
እንዲሆንልኝ ፡ ይብዛልኝ ፡ ጸጋህ
ጊዜው ፡ ደርሶ ፡ እስክደርስ ፡ አንተ ፡ ጋ
ገባ ፡ ወጣ ፡ እግሬ ፡ ሳይልብኝ ፡
ፍለጋዬ ፡ ሳትጎድል ፡ ብዛልኝ
|