From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
አስቴር ፡ አበበ (Aster Abebe)
|
|
፪ (2)
|
ሃሌሉያ (Hallelujah)
|
ዓ.ም. (Year):
|
"፳፪፬" is not in the list (፲ ፱ ፻ ፹ ፩, ፲ ፱ ፻ ፹ ፪, ፲ ፱ ፻ ፹ ፫, ፲ ፱ ፻ ፹ ፬, ፲ ፱ ፻ ፹ ፭, ፲ ፱ ፻ ፹ ፮, ፲ ፱ ፻ ፹ ፯, ፲ ፱ ፻ ፹ ፰, ፲ ፱ ፻ ፹ ፱, ፲ ፱ ፻ ፺ ፩, ...) of allowed values for the "ዓመተምህረት" property. (2024)
|
ቁጥር (Track):
|
፯ (7)
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የአስቴር ፡ አበበ ፡ አልበሞች (Albums by Aster Abebe)
|
|
ውጪ ፡ ብሎ ፡ አስወጥቶኝ ፡ ከኖርኩበት ፡ ቀዬ ፡ ሰፈር
ሊሰራብኝ ፡ ገንዘብ ፡ ሊያደርገኝ
ለእርሱ ፡ ስራ ፡ ለእርሱ ፡ ክብር
ከዳር ፡ ማድረስ ፡ ሳይችል ፡ ቀርቶ
ጥሎኝ ፡ አይሄድ ፡ በበረሀ
የአመንኩትን ፡ አውቀዋለሁ
አይቼዋለሁኝ ፡ ትናንትና (፪x)
አይቼዋለሁኝ ፡ ትናንትና (፪x)
ለነገም ፡ አመንኩት ፡ ልቤ ፡ በእርሱ ፡ ፀና
አይቼዋለሁኝ ፡ ትናንትና (፪x)
ለነገም ፡ አመንኩት ፡ ልቤ ፡ እርሱ ፡ ራር ፡ ፀና
ልቤ ፡ እርሱ ፡ ጋር ፡ ፀና (፬x)
ልቤ ፡ እርሱ ፡ ጋር ፡ ፀና
ልቤ ፡ እርሱ ፡ ጋር ፡ ፀና
ትናንት ፡ ሲደግፈኝ ፡ አይቻለሁና
ልቤ ፡ እርሱ ፡ ጋር ፡ ፀና (፪x)
ልቤ ፡ እርሱ ፡ ጋር ፡ ፀና (፪x)
ያለኝ ፡ እውነት ፡ ሆኖ ፡ እያለ
መልካምነቱንም ፡ ፍጥረት ፡ እያወቀ
እንደተረሳሁ ፡ እንደተወኝ
እንደማያየኝ ፡ እንደጣለኝ
ያ ፡ ክፉ ፡ ጠላቴ ፡ ብዙ ፡ ብዙ ፡ ዋሽቶኛል
እውነታውን ፡ ግን ፡ ቃሉ ፡ ነግሮኛል (፪)
እረዳሻለሁ ፡ አግዝሻለሁ
በፀናች ፡ ክንዴ ፡ ደግፍሻለሁ
ልብሽ ፡ ቤቴ ፡ ነው ፡ የኔ ፡ የአንቺ ፡ ነው
ለአንቺ ፡ ያለኝ ፡ ፍቅር ፡ ጥልቅ ፡ ነው
ሁኔታ ፡ የሚለው ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ነው
ቃሉ ፡ ያለኝ ፡ ግን ፡ አይዞሽ ፡ ነው
ሁኔታ ፡ የሚለው ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ነው
ቃሉ ፡ ያለኝ ፡ ግን ፡ በርቺ ፡ ነው
እረዳሻለሁ ፡ አግዝሻለሁ
በፀናች ፡ ክንዴ ፡ ደግፍሻለሁ
ልብሽ ፡ ቤቴ ፡ ነው ፡ የኔ ፡ የአንቺ ፡ ነው
ለአንቺ ፡ ያለኝ ፡ ፍቅር ፡ ጥልቅ ፡ ነው
ጠላቴ ፡ ያለው ፡ ሁሉ ፡ ውሸት ፡ ነው
ጌታ ፡ ያለኝ ፡ ግን ፡ እውነት ፡ ነው
ጠላቴ ፡ ያለው ፡ ሁሉ ፡ ውሸት ፡ ነው
ቃሉ ፡ ያለኝ ፡ ግን ፡ እውነት ፡ ነው
እቀጥላለሁ ፡ ገና ፡ እሄዳለሁ
እጁ ፡ ይዞኛል ፡ ምን ፡ እሆናለሁ
እቀጥላለሁ ፡ ገና ፡ እሄዳለሁ
ተሸክሞኛል ፡ ምን ፡ እሆናለሁ
ብዙ ፡ ብዙ ፡ መልካም ፡ ነገር
ብዙ ፡ ብዙ ፡ በጎ ፡ ነገር
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ጥሩ ፡ ነገር
ትናንቴ ፡ ላይ ፡ አርጎልኛል (፪x)
አመሰግነዋለሁ (፬)
አመሰግነዋለሁ (፬)
ቅኔዬ ፡ አልሻገተ ፡ ትውልድ ፡ አላለፈው
ገና ፡ በልጅነት ፡ በልቤ ፡ ያኖረው
ከአፉ ፡ በወጣው ፡ ቃል ፡ የተፃፈ ፡ ነገር
እርጅና ፡ አያውቀውም ፡ ይህ ፡ ሰማይ ፡ ይናገር (፪x)
አይቼዋለሁኝ ፡ ትናንትና (፪x)
ለነገም ፡ አመንኩት ፡ ልቤ ፡ በእርሱ ፡ ፀና
አይቼዋለሁኝ ፡ ትናንትና (፪x)
ለነገም ፡ አመንኩት ፡ ልቤ ፡ እርሱ ፡ ራር ፡ ፀና
ልቤ ፡ እርሱ ፡ ራር ፡ ፀና (፰x)
|