በቃኝ ፡ የማልለው (Bekagn Yemalilew) - አስቴር ፡ አበበ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አስቴር ፡ አበበ
(Aster Abebe)

Aster Abebe 2.png


(2)

ሃሌሉያ
(Hallelujah)

ዓ.ም. (Year):
"፳፪፬" is not in the list (፲ ፱ ፻ ፹ ፩, ፲ ፱ ፻ ፹ ፪, ፲ ፱ ፻ ፹ ፫, ፲ ፱ ፻ ፹ ፬, ፲ ፱ ፻ ፹ ፭, ፲ ፱ ፻ ፹ ፮, ፲ ፱ ፻ ፹ ፯, ፲ ፱ ፻ ፹ ፰, ፲ ፱ ፻ ፹ ፱, ፲ ፱ ፻ ፺ ፩, ...) of allowed values for the "ዓመተምህረት" property.
(2024)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአስቴር ፡ አበበ ፡ አልበሞች
(Albums by Aster Abebe)

እንደገና ፡ ረሃብ ፡ እንደገና ፡ ጥማት
ትናንት ፡ ምንም ፡ እንዳላየ
እንደገና ፡ ናፍቆት ፡ እንደገና ፡ ጉጉት
አንተ ፡ ወዳለህበት (፪x)

ጥቂት ፡ አንተን ፡ ቀምሶ ፡ እንደ ፡ ጠገበ ፡ ሰው
መሆን ፡ የጤና ፡ አይደለም ፡ ረሃቤን ፡ ፈውሰው
ጥቂት ፡ አንተን ፡ ቀምሶ ፡ እንደ ፡ ጠገበ ፡ ሰው
መሆን ፡ የጤና ፡ አይደለም ፡ ረሃቤን ፡ ፈውሰው

ዕለት ፡ ዕለት ፡ ባዶ ፡ ትሁንና ፡ ነፍሴ
በመገኘትህ ፡ ውስጥ ፡ ይረስርስ ፡ መንፈሴ (፪x)

በቃኝ ፡ የማልለው ፡ ይለፈኝ ፡ የማልለው
ሰለቸኝ ፡ የማልለው ፡ ያንተ ፡ ሕልውናህ
ደስታዬ ፡ ያለበት ፡ ያለፈ ፡ ሰላሜ
መገኘትህ ፡ ነው ፡ መዋያ ፡ ማደሪያዬ

ናና ፡ እስኪ ፡ አጠጣኝ
ናና ፡ እስኪ ፡ አጉርሰኝ
የእጅህን ፡ ሳይሆን ፡ ክብር ፡ መልክህን
የምድሩን ፡ ሳይሆን ፡ ሕልውናህን
ሌላውን ፡ ሳይሆን ፡ አንተው ፡ እራስህን

ናና ፡ እስኪ ፡ አጠጣኝ
ናና ፡ እስኪ ፡ አጉርሰኝ
የእጅህን ፡ ሳይሆን ፡ ክብር ፡ መልክህን
የምድሩን ፡ ሳይሆን ፡ በላይ ፡ ያለውን
ሌላውን ፡ ሳይሆን ፡ አንተው ፡ እራስህን

የፊትህን ፡ ሳይሆን ፡ ፈልጎ ፡ የእጅህን
ባትገባም ፡ ከቤቴ ፡ ላክ ፡ ብቻ ፡ ቃልህን
የእምነቱን ፡ ቁመት ፡ አድንቀህ ፡ እንዳለፍከው
አንተን ፡ በደጅ ፡ ትቶ ፡ ፈውሱን ፡ ብቻ ፡ እንዳለው

አይደል ፡ መገስገሴ ፡ ፊትህን ፡ ማለቴ
ማድጋዬን ፡ ልሞላ ፡ ላሰማምር ፡ ቤቴን
ይህን ፡ ሁሉ ፡ እንዳለ ፡ ክነዝብርቅርቁ
ካንተ ፡ ካልከተመኝ ፡ ካቆመኝ ፡ በሩቁ
ሳበኝ ፡ በእጆችህ ፡ ወደ ፡ ክብርህ ፡ ጥልቅ
አስገባኝ ፡ ከእልፍኝህ ፡ ጅምሩም ፡ ባያልቅ

በቃኝ ፡ የማልለው ፡ ይለፈኝ ፡ የማልለው
ሰለቸኝ ፡ የማልለው ፡ ያንተ ፡ ሕልውናህ
ደስታዬ ፡ ያለበት ፡ ያለፈ ፡ ሰላሜ
መገኘትህ ፡ ነው ፡ መዋያ ፡ ማደሪያዬ (፪x)