አመልክሃለው (Amelkihalehu) - አስቴር ፡ አበበ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አስቴር ፡ አበበ
(Aster Abebe)

Aster Abebe 2.png


(2)

ሃሌሉያ
(Hallelujah)

ዓ.ም. (Year):
"፳፪፬" is not in the list (፲ ፱ ፻ ፹ ፩, ፲ ፱ ፻ ፹ ፪, ፲ ፱ ፻ ፹ ፫, ፲ ፱ ፻ ፹ ፬, ፲ ፱ ፻ ፹ ፭, ፲ ፱ ፻ ፹ ፮, ፲ ፱ ፻ ፹ ፯, ፲ ፱ ፻ ፹ ፰, ፲ ፱ ፻ ፹ ፱, ፲ ፱ ፻ ፺ ፩, ...) of allowed values for the "ዓመተምህረት" property.
(2024)
ቁጥር (Track):

(6)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአስቴር ፡ አበበ ፡ አልበሞች
(Albums by Aster Abebe)

እረሳሁት ፡ ጥያቄዬን
የከበበኝን ፡ በዙሪያዬ
ስቀርብ ፡ ፊትህ ፡ ለማመስገን
ቀሎ ፡ ታየኝ ፡ ሁሉም ፡ ነገር (፪x)

ሳላመልክህ ፡ ጊዜው ፡ አይለፍ
የሚገባህን ፡ ምስጋና ፡ ሳላቀርብ
ሞልቶ ፡ ላይሞላ ፡ የምድሩ ፡ ነገር
ካልክልኝ ፡ አልጎድልም ፡ ለጭንቅ ፡ ውሎ ፡ ማደር
ርቋል ፡ ከኔ ፡ ሰፈር (፪x)

አመልክሃለው (፫x) ፡ በማደሪያዎችህ ፡ መካከል ፡ ቆሜ
አመልክሃለው (፫x) ፡ በማደሪያዎችህ ፡ መካከል ፡ ቆሜ

ለተራራው ፡ ቁመት ፡ እያልኩኝ ፡ ትልቅ ፡ ነህ
ለሸለቆው ፡ ጥልቀት ፡ እያልኩኝ ፡ ሙላት ፡ ነህ
ለሞገዱ ፡ ብርታት ፡ እያልኩኝ ፡ ሰላም ፡ ነህ
ለጨለማው ፡ ርዝመት ፡ እያልኩኝ ፡ ብርሃን ፡ ነህ

አመልክሃለው (፫x) ፡ በማደሪያዎችህ ፡ መካከል ፡ ቆሜ

ብዙ ፡ ጊዜ ፡ ታገልኩ ፡ ከቃላቶች ፡ ጋራ
ስላንተ ፡ ማንነት ፡ በዝርዝር ፡ ላወራ
አንሰው ፡ ተገኙብኝ ፡ ያለኝ ፡ ሁሉ ፡ አላረካኝ
እንደገባኝ ፡ መጠን ፡ እንኳን ፡ ልገልጽህ ፡ አቃተኝ (፪x)

ማንም ፡ እንደሚልህ ፡ አይደለህም
ከመታወቅ ፡ ታልፋለህ
እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነህ (፪x)

ትልቅ ፡ ነህ (፪x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነህ (፬x)

ካነበብኩት ፡ አይደል ፡ ከሰው ፡ የሰማሁት
ዛሬ ፡ በዚህ ፡ ሰዓት ፡ ፊትህ ፡ ያመጣሁት
ከነፍሴ ፡ ምስጋና ፡ ከውስጠቷ ፡ የሆነ
አፌን ፡ ሞልቶ ፡ የሚፈስ ፡ አዲስ ፡ ቅኔ ፡ አለ (፪x)

ያላነሰ ፡ ያላጠረ
ከላይ ፡ ከላይ ፡ ያልሆነ
ለእኔ ፡ ፍቅር ፡ ለኢየሱሴ
አለኝ ፡ ምስጋና ፡ ከነፍሴ (፪x)