ረዳቴ! (Redate!) - አሉላ ፡ ጌታሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አሉላ ፡ ጌታሁን
(Alula Getahun)

Alula Getahun 1.jpg


(1)

አስይዘኝ ፡ መስቀሉን
(Asyizegn Meskelun)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 4:09
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአሉላ ፡ ጌታሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Alula Getahun)

እንዳላየ በሚያልፍበት - የከበበኝ ይህ ሁሉ ሰው
በሞት ጥላ ስር ካለሁበት - እግዚአብሔር ነው የደረሰው! [አዝ]

“በችግሩ - ‘እግዚአብሔር ሆይ’ - ለምን ይላል - በደረቁ”
“አላየዉም - አልሰማዉም” - ብለው ሳቁ ተሳለቁ!
አምላኬ ግን - አልሰጠኝም - ለሳቁብኝ አሳልፎ
ድካሞቼን - አስወገደ - እንደጊዜው አረጋግፎ!

[አዝ]


ብዙ ሰልፎች - በነፍሴ ላይ - ሲንጓደዱ እየዋሉ
አልፎኝ ሄዷል ብዙ ጊዜ - ከንፈር መጦ ሰው ላመሉ!
“ማን ያድነኝ?” ባልኩት ጩኸት - ይነግዳል ግብዝ መንጋ
በዙሪያዬ ካሉ እጆች - የ’ሱ ብቻ ተዘረጋ!

[አዝ]


ትናንትና በደም ገንዝብ - ኑሮ አቁመው የደመቁ
አሁን የሉም ጠፋፍተዋል - እንደጤዛ አየደረቁ!
ለምለም መሳይ የጊዜያዊ - መንገዶችን በለመዱ
ዛሬ አልቀናም ተምሬያለሁ - እሄዳለሁ በመንገዱ!

[አዝ]


የሰው ልቡ ይታበያል - መነሻዉን እየረሳ
ቀን ሲያልፍለት እድል ሲያገኝ - የወደቀን አያነሳ!
በመከራ መሸሸጊያ - በክፉ ቀን የሚጠራ
እግዚአብሔር ነው ፈጥኖ ደራሽ - እንደጊዜው የሚሰራ!

[አዝ]