Agegnehu Yideg/Yetsion Teguaz Negn/Yetsion Teguaz Negn

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ አንተን ፡ ካገኘሁ ፡ ጀምሮ

ሕይወቴ ፡ በአንተ ፡ አምሮ

የፍቅርህን ፡ ብዛት ፡ አልችልም ፡ ልገልጻት

የምህረትህን ፡ ብዛት ፡ አልችልም ፡ ልገልጻት (፪x)


የፈሰሰው ፡ ሠማያዊው ፡ ፀጋ

አኑሮኛል ፡ ከአንተ ፡ ጋ

የመረጥከኝ ፡ ተባረክልኝ

የወደድከኝ ፡ ተባረክልኝ


በመስቀል ፡ ላይ ፡ ስለ ፡ እኔ ፡ ሞተሃል

አበሳዬን ፡ ወስደሃል

ምን ፡ ልክፈልህ

እንዲያው ፡ ልገዛልህ (፪x)


ሰው ፡ ያረገኝ ፡ ፀጋህ ፡ ነው

ታሪኬን ፡ ለውጦ

ከሞት ፡ አስመልጦ

ጌታ ፡ ሆይ ፡ ተመስገን (፪x)


አዝ፦ አንተን ፡ ካገኘሁ ፡ ጀምሮ

ሕይወቴ ፡ በአንተ ፡ አምሮ

የፍቅርህን ፡ ብዛት ፡ አልችልም ፡ ልገልጻት

የምህረትህን ፡ ብዛት ፡ አልችልም ፡ ልገልጻት (፪x)


የዓለም ፡ ክብር ፡ ሃብት ፡ አያጓጓኝም

ከአንተ ፡ አይበልጥብኝም

መርጬሃለሁ ፡ እከተልሃለሁ


የምህረትህ ፡ የፍቅርህ ፡ ብዛቱ

አልበረደም ፡ ግለቱ

ያዘምረኛል ፡ ተድላዬ ፡ ሆኖኛል

ያዘምረኛል ፡ ሞገሴ ፡ ሆኖኛል


ሰው ፡ ያረገኝ ፡ ፀጋህ ፡ ነው

ታሪኬን ፡ ለውጦ

ከሞት ፡ አስመልጦ

ጌታ ፡ ሆይ ፡ ተመስገን (፪x)


አዝ፦ አንተን ፡ ካገኘሁ ፡ ጀምሮ

ሕይወቴ ፡ በአንተ ፡ አምሮ

የፍቅርህን ፡ ብዛት ፡ አልችልም ፡ ልገልጻት

የምህረትህን ፡ ብዛት ፡ አልችልም ፡ ልገልጻት


በመረጥክልኝ ፡ አዲስ ፡ ህያው ፡ መንገድ

ደስ ፡ እያለኝ ፡ ልራመድ

መጨረሻዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታዬ

መጨረሻዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ጌታዬ


የሩቅ ፡ አገር ፡ የፅዮን ፡ ተጓዥ ፡ ነን

በሠማይ ፡ አገር ፡ ያለኝ

ታድያለሁ ፡ አገሬ ፡ ገባለሁ

ታድያለሁ ፡ ዘለዓለም ፡ አርፋለሁ


ሃሌሉያ


ሰው ፡ ያረገኝ ፡ ፀጋህ ፡ ነው

ታሪኬን ፡ ለውጦ

ከሞት ፡ አስመልጦ

ጌታ ፡ ሆይ ፡ ተመስገን (፪x)