From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ዓለም ፡ ስትንጫጫ ፡ ወከባ ፡ ሲበዛ
ለእኔ ፡ ግን ፡ አንተው ፡ ነህ ፡ የዘለዓለም ፡ ቤዛ
መሸሸጊያየ ፡ ነህ ፡ ይሄው ፡ አስከዛሬ
አሁንም ፡ አደራ ፡ አድርሰኝ ፡ አገሬ
(መደምደሚያየ ፡ ነህ ፡ የመጨረሻዬ
ኢየሱሴ ፡ ለእኔ ፡ ለእኔ ፡ እየሱሴ ፡ ለኔ) (፪x)
ሰው ፡ ሁሉ ፡ ይሄዳል ፡ ወደየ ፡ አምላኩ
ስዓቱ ፡ ሲያበቃ ፡ የዚች ፡ ዓለም ፡ ልኩ
ለእኔ ፡ ግን ፡ አንተው ፡ ነህ ፡ ለነፍሴ ፡ ውሳኔ
ከኃጢአት ፡ ያዳንከኝ ፡ ኢየሱስ ፡ መድህኔ
አዝ
መደምደሚያየ ፡ ነህ
በጓዳዬ ፡ ያለህ ፡ አልማዜ ፡ ንብረቴ
ለሰው ፡ የማሳይህ ፡ ትምህክቴ ፡ ኩራቴ
እውነተኛ ፡ ወዳጅ ፡ ቀን ፡ የማይለውጥህ
አነሰብኝ ፡ እኔስ ፡ እድሜዬን ፡ ብሰጥህ
አዝ
መደምደሚያየ ፡ ነህ
እየመሸ ፡ ሄደ ፡ ፀሐይ ፡ ዘቀዘቀች
ነፍሴ ፡ ግን ፡ አሁንም ፡ አንተን ፡ አለወጠች
የዚህ ፡ ዓለም ፡ ክብር ፡ ሃብት ፡ ብልጽግና
ከአንተ ፡ ዓይነጥሏትም ፡ ትኖራለች ፡ ገና
አዝ
መደምደሚያየ ፡ ነህ
11 ፡ ተራ ፡ ቁጥር ፡ ያልተዘጋጀለት
ተስፋችን ፡ ዛሬም ፡ ጌታ ፡ ነው
አይለወጥም ፡ በዙፋኑ ፡ ላይ ፡ ዓይናወጥም ፡ አሜን
እግሩ ፡ ስር ፡ ሆነን ፡ (እናመስግነው) (፪x)
ለእኛ ፡ ያረገው ፡ እጅግ ፡ (ብዙ ፡ ነው)፪
ጠላቴም ፡ አስቦኝ ፡ ጉድጓዱን ፡ ደፍኖ
ስንት ፡ ጊዜ ፡ አሻገረኝ ፡ ጌታ ፡ ድልድይ ፡ ሆኖ
በፊታችን ፡ ሆኖ ፡ እየተዋጋልን ፡
በላይ ፡ የቆመትን ፡ ወደታች ፡ ጣለልን
አዝ
ተስፋችን
አላማ ፡ ይዞ ፡ የሚያስፈራ
በአንተ ፡ ያመለጠ ፡ ከታላቅ ፡ መከራ
የሰይጣንን ፡ ምሽግ ፡ ደርምሶ ፡ ያለፈ
የአንተ ፡ ህዝብ ፡ ይኖራል ፡ ሁሌ ፡ እንዳሸነፈ
አዝ
ተስፋችን
የአምላኩ ፡ ክብር ፡ በፊቱ ፡ ያበራል
ተራራ ፡ ላይ ፡ ቆሞ ፡ መዝሙር ፡ ይዘምራል
ሞገስ ፡ ተፈራርተን ፡ አድርገንበታል
ቀናቶች ፡ ሳይቀሩ ፡ተገዝተውለታል
አዝ
ተስፋችን
|