Agegnehu Yideg/Chelemayie Bera/Lemen Eferalehu
እግዚአብሔር ፡ እያለ ፡ ለምን/እንዴት ፡ እፈራለሁ
- አምና ፡ ንም ፡ ካቻ ፡ አምና ፡ ንም ፡ ሁሉን ፡ አይቻለሁ
- አምና ፡ ንም ፡ ካቻ ፡ አምና ፡ ንም ፡ ክንዱን ፡ አይቻለሁ (፪x)
ሸለቆ ፡ ተራራው ፡ ከፍታው ፡ ዝቅታው አቤት ፡ ከእርሱ ፡ ጋራ ከፊት ፡ ከፊት ፡ ሲሄድ ፡ እጄን ፡ ይዞ ፡ እኔን ፡ እየመራ ፡ አዎ አይቸዋለሁኝ ፡ ጥበቃውን ፡ ምህረቱን ፡ ለልጁ ፡ እንዳበዛ ዛሬም ፡ ቢሆን ፡ አምነዋለሁ ፡ አይተወኝም ፡ እንዲሁ ፡ እንደ ፡ ዋዛ
- አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ እያለ ፡ ለምን ፡ እፈራለሁ
- አምና ፡ ንም ፡ ካቻ ፡ አምና ፡ ንም ፡ ክንዱን ፡ አይቻለሁ (፪x)
ከእናቱ ፡ ቤት ፡ ከአባቱ ፡ ከዘመዱ ፡ አብርሃምን ፡ ብቻውን ፡ ጠራና እኔ ፡ ወደ ፡ ማሳይህ ፡ አገር ፡ ሂድ ፡ ብሎ ፡ አዘዘውና ፡ አዎ ቃልኪዳን ፡ ገባለት ፡ ሊባርከው ፡ ለዘሩ ፡ ምድርን ፡ ሊያወርሰው እንደ ፡ ተናገርው ፡ የብዙ ፡ ህዝብ ፡ አባት ፡ አደረገው
- አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ እያለ ፡ ለምን ፡ እፈራለሁ
- አምና ፡ ንም ፡ ካቻ ፡ አምና ፡ ንም ፡ ክንዱን ፡ አይቻለሁ (፪x)
በቃሉ ፡ ተናግሮኝ ፡ ጠብቄው ፡ በፀሎቴ ፡ ምንም ፡ አልነሳኝም አባት ፡ አለኝ ፡ ብዬ ፡ ተመክቼ ፡ አላሳፈረኝም ፡ አዎ በፍፁም ፡ አልሰጋም ፡ ትደላደልኩ ፡ በአባቴ ፡ ቤት ፡ እግሬ ፡ ተተከለ ነገም ፡ ለሚሆነው ፡ አልፈራም ፡ አማኑኤል ፡ አለ
- አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ እያለ ፡ ለምን ፡ እፈራለሁ
- አምና ፡ ንም ፡ ካቻ ፡ አምና ፡ ንም ፡ ክንዱን ፡ አይቻለሁ
- አምና ፡ ንም ፡ ካቻ ፡ አምና ፡ ንም ፡ ክንዱን ፡ አይቻለሁ (፪x)
}}