Agegnehu Yideg/Bezu Yehonkelegn/Mesgana Mesgana

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ዘማሪ አገኘሁ ይደግ
ርዕስ ምሥጋና ምሥጋና

የውለታህን ልክ ቆጥሬ ቆጥሬ
መጨረስ አልቻልኩም ለአሕዛብ ተናግሬ
ያደረክልኝ ቆጥሬ ቆጥሬ
መጨረስ አልችልም በቤትህ ዘመሬ
ያደረክልኝ ቆጥሬ ቆጥሬ
መጨረስ አልችልም ለአሕዛብ ተናግሬ


ምሥጋና ምሥጋና ክብር (፪x)
ለአምላካችን ለእግዚአብሔር (፪x)
ኃጥያተኞች ሳለን እግዚአብሔር አሰበን
ከፋንዲያ ላይም ከፍ ከፍ አረገን
በሕይወት መዝገብ ላይ ሥማችንን ጻፈው
የዘለዓለም አምላክ ምሥጋና ይድረሰው
በሕይወት መዝገብ ላይ ሥማችንን ጻፈው
የናዝሬቱ ኢየሱስ ምሥጋና ይድረሰው።

አዝ

ኢየሱስ እረኛችን ጠባቂያችን ሆኗል
በሞት ጥላም ብንሄድ ምንድን ያስፈራናል?
በለመለምው መስክ በእረፍት ውኃ ዘንድ
ሁሌ ይመራናል ወደ እውነት መንገድ። (፪x)

አዝ

አዕምሮን የሚያልፍ ሰላሙን ሰጥቶናል
በጌታ በኢየሱስ ሁሌ ደስ ይለናል
ምድር ብትናውጥ አንዳች አንሆንም
የመረጠን አምላክ/ኢየሱስ/ፈጽሞ አይተወንም (፪x)

አዝ

እግዚአብሔር ከላይ በድንቅ ጐብኝቶናል
በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በእሳት አጥምቆናል
በመከራም ጊዜ እንደሰታለን
እንደ ዘንባባ ዛፍ እንለመልማለን
በመከራም ጊዜ እንደሰታለን
በሽምግልናችን እንለመልማለን።


ላመስግነው 3x
ጌታ ፍጹም ወደር የለው
ላመስግነው 3x
ውዴ ፍጹም ወደር የለው
ኢየሱስ ጌታ ነው 2x
እረ ማነው ማነው እሱን የሚመስለው
ኢየሱስ ጌታ ነው 2x
እረ ማነው ማነው ክብሩን የሚችለው
ላመስግነው 3x
ጌታ ፍጹም ወደር የለው