From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ምድር ፡ ስትጨነቅ ፡ ዘመኑ ፡ ሲከፋ
እኔ ፡ አንተን ፡ ይዣለሁ ፡ የዘለዓለም ፡ ተስፋ
በቤትህ ፡ አለሁኝ ፡ እስካሁን ፡ ተጉዤ
እየዘማመርኩኝ ፡ በገናዬን ፡ ይዤ
አዝ፦ ምን ፡ እሆናለሁ ፡ ጌታ ፡ ምን ፡ እሆናለሁ
ምን ፡ እሆናለሁ ፡ አንተን ፡ አግኝቻለሁ
ምን ፡ እሆናለሁ ፡ በቃ ፡ ምን ፡ እሆናለሁ
ምን ፡ እሆናለሁ ፡ ተደግፌሃለሁ (፭x)
ስለዚህ ፡ አመልክሃለሁ (፪x)
በቤትህ ፡ ምን ፡ አጥቻለሁ ፡ ገና ፡ እኖራለሁ
ማረፊያ ፡ አንተ ፡ ነህ (፫x)
ተጠለልኩ ፡ በጥላህ
ማረፊያ ፡ አንተ ፡ ነህ (፫x)
ተመካሁ ፡ በሥምህ
ምን ፡ ይዋጠኝ ፡ ለኑሮዬ ፡ አልሰጋም
የጐደለኝ ፡ የለም ፡ አንተን ፡ ከተጠጋሁ
በሰላም ፡ ወጥቼ ፡ በሰላም ፡ ገባለሁ
ዓለም ፡ የሌላትን ፡ ሰላም ፡ አግኝቻለሁ
አዝ፦ ምን ፡ እሆናለሁ ፡ ጌታ ፡ ምን ፡ እሆናለሁ
ምን ፡ እሆናለሁ ፡ አንተን ፡ አግኝቻለሁ
ምን ፡ እሆናለሁ ፡ በቃ ፡ ምን ፡ እሆናለሁ
ምን ፡ እሆናለሁ ፡ ተደግፌሃለሁ (፭x)
ስለዚህ ፡ አመልክሃለሁ (፪x)
በቤትህ ፡ ምን ፡ አጥቻለሁ ፡ ገና ፡ እኖራለሁ
ማረፊያ ፡ አንተ ፡ ነህ (፫x)
ተመካሁ ፡ በሥምህ
የዚህ ፡ ዓለም ፡ ሰዎች ፡ በሚያልፈው ፡ ሲመኩ
የሰውን ፡ ማንነት ፡ በገንዘብ ፡ ሲለኩ
እኔ ፡ ግን ፡ በአንተ ፡ ልመካ ፡ በማታልፈው ፡ ጌታ
ስለምታዋጣኝ ፡ የማታ ፡ ማታ
አዝ፦ ምን ፡ እሆናለሁ ፡ ጌታ ፡ ምን ፡ እሆናለሁ
ምን ፡ እሆናለሁ ፡ አንተን ፡ አግኝቻለሁ
ምን ፡ እሆናለሁ ፡ በቃ ፡ ምን ፡ እሆናለሁ
ምን ፡ እሆናለሁ ፡ ተደግፌሃለሁ (፭x)
|