From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
ይወራ ፡ ይነገር ፡ የአምላኬ ፡ ክብር
ይወደስ ፡ ይወደስ
ከቶ ፡ ማነው ፡ እርሱ ፡ አምላኬን ፡ የሚደርስ
ኧረ ፡ ማነው ፡ ደርሶ ፡ አባቴን ፡ የሚደርሰው
ማነው (፫x) ፡ ኃይልህን ፡ የሚችለው
ማነው (፫x) ፡ ግርማህን ፡ የሚችለው
ኃይልህን ፡ የሚችለው ፡ ግርማህን ፡ የሚችለው (፪x)
አዝ፦ ሁሉን ፡ ታደርግ ፡ ዘንድ ፡ ቻይ ፡ ነህ
ሃሳብህ ፡ አይከለከልም
አቤት ፡ የእኛ ፡ ጌታ ፡ ቋጠሮን ፡ የምትፈታ
አቤት ፡ የእኛ ፡ ጌታ ፡ ጥያቄን ፡ የምትመልስ
ያስጨነቀን ፡ ተመታ ፡ ሌት ፡ ተቀን ፡ ያናወጠን
በደስታ ፡ እንዳናመልክህ ፡ በሀዘን ፡ ያስቀመጠን
አሁን ፡ ግን ፡ ደስ ፡ ብሎናል
ከእስራትም ፡ ተፈተናል
ጌታችን ፡ እውነትም ፡ ጌታ
ድል ፡ የአንተ ፡ የማታ ፡ ማታ
ኢየሱስ ፡ ብቻህን ፡ ጌታ
አዝ፦ ሁሉን ፡ ታደርግ ፡ ዘንድ ፡ ቻይ ፡ ነህ
ሃሳብህ ፡ አይከለከልም
አቤት ፡ የእኛ ፡ ጌታ ፡ ቋጠሮን ፡ የምትፈታ
አቤት ፡ የእኛ ፡ ጌታ ፡ ጥያቄን ፡ የምትመልስ
አይሁድ ፡ ሁሉ ፡ እንዲጠፋ ፡ የሞት ፡ አዋጅ ፡ ታወጀ
መርደኪዮስ ፡ እንዲሰቀል ፡ መስቀያ ፡ ተዘጋጀ
እጅህ ፡ ግን ፡ ቀድሞ ፡ ደረሰ
የሃማ ፡ ምክሩ ፡ ፈረሰ
ወጥመዱ ፡ እራሱን ፡ ያዘው
ሕዝብህን ፡ ክብር ፡ አለበስከው
ባሪያህን ፡ ክብር ፡ አለበስከው
ማነው (፫x) ፡ ኃይልህን ፡ የሚችለው
ማነው (፫x) ፡ ግርማህን ፡ የሚችለው
ኃይልህን ፡ የሚችለው ፡ ግርማህን ፡ የሚችለው (፪x)
አለቁ ፡ ጠፉ ፡ ብሎ ፡ ጠላት ፡ ወሬ ፡ ሲያወራ
ሥማችንን ፡ ሲያጠፋ ፡ ክፉ ፡ ዘርን ፡ ሲዘራ
ሥማችንን ፡ አደስክልን
ግርማ ፡ መለስክልን
በፊቱ ፡ ዘይት ፡ ቀባኸን
በእጥፍ ፡ ፀጋን ፡ ሰጠኸን (፪x)
ማነው (፫x) ፡ ኃይልህን ፡ የሚችለው
ማነው (፫x) ፡ ግርማህን ፡ የሚችለው
ኃይልህን ፡ የሚችለው ፡ ግርማህን ፡ የሚችለው (፪x)
አዝ፦ ሁሉን ፡ ታደርግ ፡ ዘንድ ፡ ቻይ ፡ ነህ
ሃሳብህ ፡ አይከለከልም
አቤት ፡ የእኛ ፡ ጌታ ፡ ቋጠሮን ፡ የምትፈታ
አቤት ፡ የእኛ ፡ ጌታ ፡ ጥያቄን ፡ የምትመልስ (፪x)
|