From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
እስካሁን ፡ እንዳየሁ ፡ በዕድሜ ፡ ዘመኔ
ማንም ፡ አላገኘሁ ፡ እንዳንተ ፡ ለእኔ
እናትና ፡ አባት ፡ ጓደኛ ፡ ሆንክልኝ
ማንም ፡ ያልሰማውን ፡ ሚስጥሬን ፡ ያስክልኝ
አዝ፦ እንዳልበድልህ ፡ ጠብቀኝ
እንዳላሳዝንህ ፡ ጠብቀኝ
እኔ ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ማንም ፡ የለኝ
እንዳልበድልህ ፡ ጠብቀኝ
እንዳላሳዝንህ ፡ ጠብቀኝ
ወዳጄ ፡ ካለ ፡ አንተ ፡ ማንም ፡ የለኝ
እንዳልበድልህ ፡ ጠብቀኝ
እንዳላሳዝንህ ፡ ጠብቀኝ
አንተን ፡ ችላ ፡ ያልሁ ፡ ፀጋ ፡ ሲርቃቸው
አይቻለሁ ፡ ጌታ ፡ ቀን ፡ ሲመሽባቸው
እስካሁን ፡ ያለፍኩት ፡ ሸለቆ ፡ ተራራ
ምን ፡ ይውጠኝ ፡ ነበር ፡ ባልሆን ፡ ከአንተ ፡ ጋራ
አዝ፦ እንዳልበድልህ ፡ ጠብቀኝ
እንዳላሳዝንህ ፡ ጠብቀኝ
እኔ ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ማንም ፡ የለኝ
እንዳልበድልህ ፡ እንዳላሳዝንህ ፡ ጠብቀኝ
ባለፈው ፡ ዘመኔስ ፡ ብዙ ፡ አጥፍቻለሁ
ባለማስተዋሌም ፡ ተጐድቻለሁ
ፍቅርን ፡ የተሞላህ ፡ ባታግዘኝ ፡ ኖሮ
እንዴት ፡ ይዘለቃል ፡ የዚህ ፡ ምድር ፡ ኑሮ
አሁንም ፡ ጌታዬ ፡ መንገዴን ፡ አደራ
ታዳጊ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ በሚያገኘኝ/በሚገጥመኝ ፡ መከራ (፪x)
መንገዴን ፡ አደራ ፡ አደራ
በቀረው ፡ ጉዞዬ ፡ ኢየሱስ
ሥራህን ፡ ሥራ ፡ (ሥራህን ፡ ሥራ) (፪x)
ጉዞዬ ፡ ከብዶብኝ ፡ ስወድቅ ፡ ስነሳ
እዚህ ፡ ደርሻለሁ ፡ በብዙ ፡ አበሳ
የቀረው ፡ ዘመኔስ ፡ ብሩክ ፡ ይሁንልኝ
ጌታዬ ፡ በኃይልህ ፡ ሥራህን ፡ ሥራልኝ
የኋላዬን ፡ ልርሳ ፡ ወደ ፡ አንተው ፡ ልጠጋ
ከፊቴ ፡ ያለውን ፡ . (1) . ፡ ዘርጋ (፪x)
መንገዴን ፡ አደራ ፡ አደራ
በቀረው ፡ ዘመኔ ፡ ኢየሱስ
ሥራህን ፡ ሥራ ፡ (ሥራህን ፡ ሥራ) (፪x)
ለሥጋዬ ፡ ምኞት ፡ በከንቱ ፡ ስገዛ
ስንት ፡ ጊዜ ፡ አቃጠልኩ ፡ እንዲሁ ፡ በዋዛ
ለቅዱሱ ፡ አደራ ፡ ታማኝ ፡ አልነበርኩም
እንደ ፡ ልብህ ፡ ደስታም ፡ አላገለገልኩም
ከእንግዲህስ ፡ ጌታ ፡ ሥራብኝ ፡ እንደ ፡ ሰው
በጭንጋፉ/በትንሹ ፡ ባሪያ ፡ ከሁሉም ፡ በማንሰው (፪x)
መንገዴን ፡ አደራ ፡ አደራ
በቀረው ፡ ዘመኔ ፡ ኢየሱስ
ሥራህን ፡ ሥራ ፡ (ሥራህን ፡ ሥራ) (፪x)
|