From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
|
|
|
ልዩ ፡ እትም (Esp)
|
ብዙ ፡ የሆንክልኝ (Bezu Yehonkelegn)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፳ ፻ ፩ (2009)
|
ቁጥር (Track):
|
፪ (2)
|
ርዝመት (Len.):
|
7:28
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የ{{{ዘማሪ}}} ፡ አልበሞች (Albums by {{{Artist}}})
|
|
ክብሬ ፡ ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ጌታዬ
በመስቀልህ ፡ የሞትከው ፡ ባለውለታዬ
ክብሬ ፡ ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ጌታዬ
ብዙ ፡ የሆንክልኝ ፡ ባለውለታዬ
ጌታዬ ፡ ጌታዬ ፡ ጌታዬ (፬x)
አዝ፦ ውለታው (፫x)
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
እግዚአብሔር ፡ አምላኬ ፡ ድንቅ ፡ አደረገልኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ውለታው (፫x)
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ናዝራዊው ፡ ወዳጄ ፡ ብዙ ፡ አደረገልኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ኢየሱሴ ፡ ለእኔ ፡ በመስቀል ፡ ሞተልኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
በእንጨት ፡ ተንጠልጥሎ ፡ እርግማን ፡ ሆነልኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
በከበረ ፡ ደሙ ፡ በውድ ፡ ዋጋ ፡ ገዛኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ሲጠራኝ ፡ ብቻዬን ፡ ዛሬ ፡ ግን ፡ አበዛኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ከአይምሮ ፡ በላይ ፡ ነው ፡ የእርሱ ፡ ውለታ
እንዴት ፡ ላመስግነው ፡ ይህንን ፡ ጌታ
እጅግ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ የእርሱ ፡ ውለታ
እንዴት ፡ ላመስግነው ፡ ይህንን ፡ ጌታ
አዝ፦ ውለታው (፫x)
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
እግዚአብሔር ፡ አምላኬ ፡ ድንቅ ፡ አደረገልኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ውለታው (፫x)
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ናዝራዊው ፡ ወዳጄ ፡ ብዙ ፡ አደረገልኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ከበለስ ፡ ዛፍ ፡ በታች ፡ ተቀምጬ ፡ አይኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ተንኮል ፡ የሌለብህ ፡ የእስራኤል ፡ ልጅ ፡ አለኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ታማኝ ፡ አድርጐ ፡ ቆጥሮ ፡ ለአገልግሎት ፡ ሾመኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ኢየሱሴን ፡ መጠጋት ፡ ለእኔ ፡ እጅግ ፡ ጠቀመኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ከአይምሮ ፡ በላይ ፡ ነው ፡ የእርሱ ፡ ውለታ
እንዴት ፡ ላመስግነው ፡ ይህንን ፡ ጌታ
እጅግ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ የእርሱ ፡ ውለታ
እንዴት ፡ ላመስግነው ፡ ይህንን ፡ ጌታ
አዝ፦ ውለታው (፫x)
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
እግዚአብሔር ፡ አምላኬ ፡ ድንቅ ፡ አደረገልኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ውለታው (፫x)
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ናዝራዊው ፡ ወዳጄ ፡ ብዙ ፡ አደረገልኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
በግ ፡ እረኛ ፡ ነብረኩ ፡ ገና ፡ ብላቴና
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
እግዚአብሔር ፡ ፊት ፡ ሞገስ ፡ አገኘሁኝና
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
እኔን ፡ በናቁኝ ፡ ፊት ፡ ራሴን ፡ በዘይት ፡ ቀባኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ንጉሡ ፡ ሊያከብረኝ ፡ ወደ ፡ እልፊኙ ፡ አገባኝ
(ውለታው ፡ በዛብኝ)
ሰው ፡ ላደረገልኝ ፡ እንደዚህ ፡ ዛሬ
ሥሙን ፡ ላወድሰው ፡ በዝማሬ
እጅግ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ የእርሱ ፡ ውለታ
እንዴት ፡ ላመስግነው ፡ ይህንን ፡ ጌታ
እንዴት ፡ ላመስግነው ፡ ይህንን ፡ ጌታ (፬x)
ክብሬ ፡ ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ጌታዬ
በመስቀልህ ፡ የሞትከው ፡ ባለውለታዬ
ክብሬ ፡ ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ጌታዬ
ብዙ ፡ የሆንክልኝ ፡ ባለውለታዬ
ጌታዬ ፡ ጌታዬ ፡ ጌታዬ (፬x)
|