Agegnehu Yideg/Bezu Yehonkelegn/Anten Anten Alech
ዘማሪ አገኘሁ ይደግ
ርዕስ አንተን አንተን አለች
አልበም ብዙ የሆንክልኝ
በእንባ አንተኑ ደጅ ልጥና
በልጅህ አትጨክንምና
በእንባ አባቴን ደጅ ልጥና
ሌላ የለኝምና (፪x)
አትጨክንምና ሌላ የለኝምና (፪x)
ከምድረ በዳው ኑሮ ከዛ ከቃጠሎ
አንተ ነህ የታደካት ደርሰህላት ቶሎ
ስለዚህም ነፍሴ አንተን አንተን አለች
ቀንና ሌሊት ፊትህን ፈለገች
አዝ
ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደምትናፍቅ
ነፍሴ አንተን አንተን አለች (፬x)
ኢየሱስ አንተ ነህ ለነፍሴ ትርጉሟ
እውነተኛ ወዳጅ የኑሮ ጣዕሟ
ያለ አንተ መኖር አይሆንላትም
መጠጊያ ጐጆ ሌላ የላትም
አዝ
ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደምትናፍቅ
ነፍሴ አንተን አንተን አለች (፬x)
ባስለመድከኝ ስፍራ እጠብቅሃለሁ
አንተን ካላገኘሁ መቼ እተኛለሁ
ሌሊቱ ጭር ብሏል ሰው ሁሉ ተኝቷል
ከአንተ ጋር መሆኑ ነፍሴ ግን አምሯታል
አዝ
ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደምትናፍቅ
ነፍሴ አንተን አንተን አለች (፬x)
እግዚአብሔር አለቴ እመካብሃለሁ
እስከ ዘለዓለሙ ተስፋ አደርግሃልሁ
ምንም ሳትሰራልህ ነፍሴን ወደሃታል
ለቀሪውስ ጉዞ ምንድን ያሰጋታል
በእንባ አንተኑ ደጅ ልጥና
በልጅህ አትጨክንምና
በእንባ አባቴን ደጅ ልጥና
ሌላ የለኝምና (፪x)
አትጨክንምና ሌላ የለኝምና (፬x)