Agegnehu Yideg/Bezu Yehonkelegn/Anten Anten Alech

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ዘማሪ አገኘሁ ይደግ ርዕስ አንተን አንተን አለች አልበም ብዙ የሆንክልኝ

በእንባ አንተኑ ደጅ ልጥና በልጅህ አትጨክንምና በእንባ አባቴን ደጅ ልጥና ሌላ የለኝምና (፪x)

አትጨክንምና ሌላ የለኝምና (፪x)

ከምድረ በዳው ኑሮ ከዛ ከቃጠሎ አንተ ነህ የታደካት ደርሰህላት ቶሎ ስለዚህም ነፍሴ አንተን አንተን አለች ቀንና ሌሊት ፊትህን ፈለገች

አዝ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደምትናፍቅ ነፍሴ አንተን አንተን አለች (፬x)

ኢየሱስ አንተ ነህ ለነፍሴ ትርጉሟ እውነተኛ ወዳጅ የኑሮ ጣዕሟ ያለ አንተ መኖር አይሆንላትም መጠጊያ ጐጆ ሌላ የላትም

አዝ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደምትናፍቅ ነፍሴ አንተን አንተን አለች (፬x)

ባስለመድከኝ ስፍራ እጠብቅሃለሁ አንተን ካላገኘሁ መቼ እተኛለሁ ሌሊቱ ጭር ብሏል ሰው ሁሉ ተኝቷል ከአንተ ጋር መሆኑ ነፍሴ ግን አምሯታል

አዝ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደምትናፍቅ ነፍሴ አንተን አንተን አለች (፬x)

እግዚአብሔር አለቴ እመካብሃለሁ እስከ ዘለዓለሙ ተስፋ አደርግሃልሁ ምንም ሳትሰራልህ ነፍሴን ወደሃታል ለቀሪውስ ጉዞ ምንድን ያሰጋታል

በእንባ አንተኑ ደጅ ልጥና በልጅህ አትጨክንምና በእንባ አባቴን ደጅ ልጥና ሌላ የለኝምና (፪x) አትጨክንምና ሌላ የለኝምና (፬x)