Addisu Worku/Yemesqelu Feqer/Nuro Kegieta Gar Temognal
ኑሮ ፡ ከጌታ ፡ ጋር ፡ ጥሞኛል
ከምለየው ፡ ሞት ፡ ይሻለኛል
ይወደኛል ፡ እወደዋለሁ
ሚስጢሬን ፡ አካፍለዋለሁ
- ወዶኝ ፡ ቀርቧል ፡ ወደ ፡ ልቤ
- ነፍሴን ፡ አጥግቧል ፡ ተርቤ
- ሌላ ፡ ጌታ ፡ አያሻኝም
- እንደእርሱ ፡ አይሆንልኝም
- አዝ፦ ስሙ ፡ ይክበር ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ የእኔ ፡ የግሌ ፡ መከታ
- ከመከራ ፡ ያወጣኛል ፡ እጁን ፡ ልኮ ፡ ያድነኛል
- ስሙ ፡ ይክበር (፪x)
ወንድም ፡ ጋሻዬ ፡ እርሱ ፡ ነው
ታማኝ ፡ ጓዴ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው
በመከራ ፡ ያጸናኛል ፡ በደስታው ፡ ይሞላኛል
- ልቤን ፡ በፍቅሩ ፡ ያከታል
- ጠላቴን ፡ ይቀጠቅጣል
- እስከሞቴ ፡ አልተወውም
- ስሙን ፡ ጠርቼ ፡ አልጠግብም
- አዝ፦ ስሙ ፡ ይክበር ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ የእኔ ፡ የግሌ ፡ መከታ
- ከመከራ ፡ ያወጣኛል ፡ እጁን ፡ ልኮ ፡ ያድነኛል
- ስሙ ፡ ይክበር (፪x)
ሳለቅስ ፡ እምባዬን ፡ ያብሳል
ከወላጅ ፡ እናት ፡ ይብሳል
ለዘለዓለም ፡ አይለይም
ስሙን ፡ ጠርቼ ፡ አልጠግብም
- የድሆች ፡ አባት ፡ እርሱ ፡ ነው
- ጉስቁልናን ፡ የቀመሰው
- መሪአችን ፡ ነው ፡ አለቃችን
- እናክብረው ፡ አባታችን
አዝ
ስሙ ይክበር የእኔ ጌታ የእኔ የግሌ መከታ
ከመከራ ያወጣኛል እጁን ልኮ ያድነኛል
ስሙ ይክበር (፪x)
ስሙ ይክበር (፫x)