Addisu Worku/Yemesqelu Feqer/Nuro Kegieta Gar Temognal

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ


ኑሮ ፡ ከጌታ ፡ ጋር ፡ ጥሞኛል
ከምለየው ፡ ሞት ፡ ይሻለኛል
ይወደኛል ፡ እወደዋለሁ
ሚስጢሬን ፡ አካፍለዋለሁ

ወዶኝ ፡ ቀርቧል ፡ ወደ ፡ ልቤ
ነፍሴን ፡ አጥግቧል ፡ ተርቤ
ሌላ ፡ ጌታ ፡ አያሻኝም
እንደእርሱ ፡ አይሆንልኝም


አዝ፦ ስሙ ፡ ይክበር ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ የእኔ ፡ የግሌ ፡ መከታ
ከመከራ ፡ ያወጣኛል ፡ እጁን ፡ ልኮ ፡ ያድነኛል
ስሙ ፡ ይክበር (፪x)


ወንድም ፡ ጋሻዬ ፡ እርሱ ፡ ነው
ታማኝ ፡ ጓዴ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው
በመከራ ፡ ያጸናኛል ፡ በደስታው ፡ ይሞላኛል

ልቤን ፡ በፍቅሩ ፡ ያከታል
ጠላቴን ፡ ይቀጠቅጣል
እስከሞቴ ፡ አልተወውም
ስሙን ፡ ጠርቼ ፡ አልጠግብም


አዝ፦ ስሙ ፡ ይክበር ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ የእኔ ፡ የግሌ ፡ መከታ
ከመከራ ፡ ያወጣኛል ፡ እጁን ፡ ልኮ ፡ ያድነኛል
ስሙ ፡ ይክበር (፪x)


ሳለቅስ ፡ እምባዬን ፡ ያብሳል
ከወላጅ ፡ እናት ፡ ይብሳል
ለዘለዓለም ፡ አይለይም
ስሙን ፡ ጠርቼ ፡ አልጠግብም

የድሆች ፡ አባት ፡ እርሱ ፡ ነው
ጉስቁልናን ፡ የቀመሰው
መሪአችን ፡ ነው ፡ አለቃችን
እናክብረው ፡ አባታችን


አዝ ስሙ ይክበር የእኔ ጌታ የእኔ የግሌ መከታ
ከመከራ ያወጣኛል እጁን ልኮ ያድነኛል
ስሙ ይክበር (፪x)

ስሙ ይክበር (፫x)