ኑሮ ፡ ከጌታ ፡ ጋር ፡ ጥሞኛል (Nuro Kegieta Gar Temognal) - አዲሱ ፡ ወርቁ

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
አዲሱ ፡ ወርቁ
(Addisu Worku)

Addisu Worku 1.png


(1)

ክቡር ፡ ክቡር
(Kebur Kebur)

ቁጥር (Track):

(10)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲሱ ፡ ወርቁ ፡ አልበሞች
(Albums by Addisu Worku)

 
ኑሮ ፡ ከጌታ ፡ ጋር ፡ ጥሞኛል
ከምለየው ፡ ሞት ፡ ይሻለኛል
ይወደኛል ፡ እወደዋለሁ
ሚስጢሬን ፡ አካፍለዋለሁ
ወዶኝ ፡ ቀርቧል ፡ ወደ ፡ ልቤ
ነፍሴን ፡ አጥግቧል ፡ ተርቤ
ሌላ ፡ ጌታ ፡ አያሻኝም
እንደእርሱ ፡ አይሆንልኝም

አዝ፦ ስሙ ፡ ይክበር ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ የእኔ ፡ የግሌ ፡ መከታ
ከመከራ ፡ ያወጣኛል ፡ እጁን ፡ ልኮ ፡ ያድነኛል
ስሙ ፡ ይክበር (፪x)

ወንድም ፡ ጋሻዬ ፡ እርሱ ፡ ነው
ታማኝ ፡ ጓዴ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው
በመከራ ፡ ያጸናኛል ፡ በደስታው ፡ ይሞላኛል
ልቤን ፡ በፍቅሩ ፡ ያከታል
ጠላቴን ፡ ይቀጠቅጣል
እስከሞቴ ፡ አልተወውም
ስሙን ፡ ጠርቼ ፡ አልጠግብም

አዝ፦ ስሙ ፡ ይክበር ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ የእኔ ፡ የግሌ ፡ መከታ
ከመከራ ፡ ያወጣኛል ፡ እጁን ፡ ልኮ ፡ ያድነኛል
ስሙ ፡ ይክበር (፪x)

ሳለቅስ ፡ እምባዬን ፡ ያብሳል
ከወላጅ ፡ እናት ፡ ይብሳል
ለዘለዓለም ፡ አይለይም
ስሙን ፡ ጠርቼ ፡ አልጠግብም
የድሆች ፡ አባት ፡ እርሱ ፡ ነው
ጉስቁልናን ፡ የቀመሰው
መሪአችን ፡ ነው ፡ አለቃችን
እናክብረው ፡ አባታችን

አዝ፦ ስሙ ፡ ይክበር ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ የእኔ ፡ የግሌ ፡ መከታ
ከመከራ ፡ ያወጣኛል ፡ እጁን ፡ ልኮ ፡ ያድነኛል
ስሙ ፡ ይክበር (፪x)

ስሙ ፡ ይክበር (፫x)