From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ምሥጋና ፡ ምሥጋና ፡ ለኢየሱስ ፡ ምሥጋና
ይገባሃል ፡ አምላክ ፡ ለአንተ ፡ ለሆንከው ፡ ገናና (፪x)
መከራ ፡ እንደሚያልፍ ፡ የጊዜውም ፡ ሃዘን
እንደምንራመድ ፡ ሁሉን ፡ ነገር ፡ አልፈን
ለቅሶ ፡ በዝማሬ ፡ ሃዘን ፡ በደስታ
እንደሚለወጡ ፡ ተናግሯል ፡ ያ ፡ ጌታ
አዝ፦ ምሥጋና ፡ ምሥጋና ፡ ለኢየሱስ ፡ ምሥጋና
ይገባሃል ፡ አምላክ ፡ ለአንተ ፡ ለሆንከው ፡ ገናና (፪x)
እንደበደላችን ፡ አልተከፈለንም
ጌታ ፡ በመዓቱ ፡ አልተናኘንም
ምህረትን ፡ የሚወድ ፡ የሰራዊት ፡ ጌታ
እንዳዬን ፡ ለመክፈል ፡ በውርደት ፡ ተመታ
አዝ፦ ምሥጋና ፡ ምሥጋና ፡ ለኢየሱስ ፡ ምሥጋና
ይገባሃል ፡ አምላክ ፡ ለአንተ ፡ ለሆንከው ፡ ገናና (፪x)
በኑሮዬ ፡ ሁሉ ፡ አንተን ፡ አስከብሬ
በመከራ ፡ ልለፍ ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ አብሬ
የሕይወት ፡ እስትንፋስ ፡ ሰጥተኸኛልና
መስዋዕቴ ፡ ይኸው ፡ ከነፍሴ ፡ ምሥጋና
አዝ፦ ምሥጋና ፡ ምሥጋና ፡ ለኢየሱስ ፡ ምሥጋና
ይገባሃል ፡ አምላክ ፡ ለአንተ ፡ ለሆንከው ፡ ገናና (፪x)
|