From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
በሞት ፡ ጥላ ፡ የሚያድር ፡ በግዞች ፡ ሸለቆ
ጠላት ፡ የሚመታው ፡ አሸምቆ
ከአንበሳው ፡ መንጋጋ ፡ ለጣር ፡ የተጣለ
ነበር ፡ ወገኔ ፡ የቆሰለ
አዝ፦ ከሞትም ፡ ያድነዋል ፡ ከሞትም ፡ ያድናል
ከሞትም ፡ ያድናል ፡ ኢየሱስ (፪x)
ጌታ ፡ ደርሶለታል ፡ ወንጌል ፡ ልኮለታል
ሰማያዊው ፡ ብርሃን ፡ በርቶለታል
መልዕክተኞች ፡ ወጡ ፡ ጠላትን ፡ ገጠሙ
በመስቀሉ ፡ ጉልበት ፡ ድል ፡ አደረጉት
አዝ፦ ከሞትም ፡ ያድነዋል ፡ ከሞትም ፡ ያድናል
ከሞትም ፡ ያድናል ፡ ኢየሱስ (፪x)
ዓለምና ፡ ትርፏን ፡ ወደ ፡ ኋላ ፡ ገፍቶ
ከመታወቅ ፡ ይልቅ ፡ መናቅ ፡ መርጦ
ዘሩን ፡ ተሸክሞ ፡ በለቅሶ ፡ የሚዘራ
በደስታ ፡ ያጭዳል ፡ ከአምላክ ፡ ጋራ
አዝ፦ ከሞትም ፡ ያድነዋል ፡ ከሞትም ፡ ያድናል
ከሞትም ፡ ያድናል ፡ ኢየሱስ (፬x)
|