ኢየሱስ (Eyesus) - አዲሱ ፡ ወርቁ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲሱ ፡ ወርቁ
(Addisu Worku)

Addisu Worku 1.png


(1)

የመስቀሉ ፡ ፍቅር
(Yemesqelu Feqer)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2006)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 3:39
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲሱ ፡ ወርቁ ፡ አልበሞች
(Albums by Addisu Worku)

ኑሮ ፡ ያለ ፡ ጌታ ፡ ታክቶኝ ፡ ኀጢአቴ ፡ አስመርሮኝ
ወደ ፡ ኢየሱሴ ፡ ብመለስ ፡ የእርሱ ፡ ደግነት ፡ ማርኮኝ
በድል ፡ ጐዳና ፡ ብገባ ፡ ፍቅሩ ፡ ነፍሴን ፡ ብትፈታ
ጉልበቴን ፡ ለጠላት ፡ ላልሰጥ ፡ ቃል ፡ ገባሁኝ ፡ ለጌታ

በመከራና ፡ በጭንቀትም ፡ ሁሉ ፡ ጌታን ፡ አመልከዋለሁ
ኑሮ ፡ ያለእርሱ ፡ ጉዳት ፡ ነው ፡ ከእርሱ ፡ ጋር ፡ ግን ፡ ደስታ
የመልካም ፡ ሁሉ ፡ መሰረት ፡ ይመስገን ፡ የእኛ ፡ ጌታ
ስንጨነቅ ፡ የሚራራ ፡ ስንደክም ፡ ደጋፊያችን
በበረሃ ፡ ዓለም ፡ እያለን ፡ ስንጠማ ፡ እርካታችን
ዞሮ ፡ መግቢያችን ፡ ኢየሱስ ፡ ማረፊያችን ፡ አንተ ፡ ነህ
ብንከዳህ ፡ አያዋጣንም ፡ የድሃ ፡ ጐጇችን ፡ ነህ

ጌታ ፡ ጌታችን ፡ ጌታችን ፡ አስታውሰን (፪x)
ብለን ፡ ተጣርተን ፡ ሳናፍር ፡ እስካሁን ፡ ተጉዘናል
በነገር ፡ ሁሉ ፡ መጽናትን ፡ ከጌታ ፡ ተምረናል
የሚያሳፍር ፡ ስም ፡ አይደለም ፡ የሰጠኸን ፡ ጌታችን
ክርስቲያን ፡ ጀግንነት ፡ እንደው ፡ ይረዳልን ፡ ልባችን
ክፉውን ፡ ሁሉ ፡ ተቃውመን ፡ ከኀጢአት ፡ ጋራ ፡ ታግለን
ጉዟችን ፡ በድል ፡ ያከትማል ፡ የጌታን ፡ መስቀል ፡ ይዘን

ክብር ፡ ክብር ፡ ሃሌ ፡ ሉያ (፪x)
የነፍሳት ፡ ሁሉ ፡ ምሥጋና ፡ ዙፋንህን ፡ ይክበበው
በቸርነትህ ፡ ተገርሟል ፡ በልጅህ ፡ የዋጀኸው (፪x)