የእኔ ፡ መድህን ፡ ጌታ (Yenie Medhen Gieta) - አዲሱ ፡ ወርቁ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲሱ ፡ ወርቁ
(Addisu Worku)

Addisu Worku 2.jpeg


(2)

አንዴ ፡ ቆርጠናል
(Andie Qortenal)

ዓ.ም. (Year): ፲፱፻፺፱ (2007)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲሱ ፡ ወርቁ ፡ አልበሞች
(Albums by Addisu Worku)

አምላኬን ፡ ልባርክ ፡ አፌን ፡ እከፍታለሁ
ለወደደኝ ፡ ጌታ ፡ ምስጋናን ፡ እሰዋለሁ ፡ ተመስገን ፡ እላለሁ
በመከራ ፡ ጊዜ ፡ ፈጥኖ ፡ ደርሶልኛል
ነፍሴ ፡ ትገዛለት ፡ ፍቅሩ ፡ አሸንፎኛል (፪x)

ለመድህኔ ፡ ይሁን ፡ ምስጋና
ድሃ ፡ አደጉን ፡ አስቧልና
የሚያረካ ፡ ፈጸሞ ፡ በአለም
እንደ ፡ ኢየሱስ ፡ የለም

አዝ:- ሰማይ ፡ ዙፋኑ ፡ መቀመጫው
ምድርም ፡ ለእግሮቹ ፡ መረገጫ
ስሙ ፡ ምን ፡ ጊዜም ፡ የሚረታ
ትላንትም ፡ ዛሬም ፡ ነገም ፡ ጌታ
የእኔ ፡ መድህን ፡ ጌታ

ብርቱ ፡ መታጠቂያው ፡ ድንገት ፡ ሲላላበት
የጦረኛው ፡ መውጊያው ፡ ጦር ፡ ሲሰበርበት (፪x)
ተከላካይ ፡ ጋሻው ፡ ከእጁ ፡ ሲወድቅበት
መከታ ፡ ነው ፡ ያለው ፡ ተገኔ ፡ ነው ፡ ያለው ፡ ምሽግ ፡ ሲናድበት

መድህኔ ፡ ግን ፡ ሁሌ ፡ ባለ ፡ ድል
ድል ፡ አድራጊ ፡ ክንዱ ፡ የማይዝል
ታላቅ ፡ አምላክ ፡ የኔ ፡ መከታ
ሁሌ ፡ የሚረታ

አዝ:- ሰማይ ፡ ዙፋኑ ፡ መቀመጫው
ምድርም ፡ ለእግሮቹ ፡ መረገጫ
ስሙ ፡ ምንጊዜም ፡ የሚረታ
ትላንትም ፡ ዛሬም ፡ ነገም ፡ ጌታ
የእኔ ፡ መድህን ፡ ጌታ

ሆ ፡ እየተባለ ፡ ተስፋ ፡ የተጣለበት
በጊዜው ፡ የሰው ፡ ልጅ ፡ የተጋደለበት ፡ የተራረደበት
ዛሬ ፡ ተረት ፡ ሆኖ ፡ በትዝብት ፡ ይወራል
የኢየሱስ ፡ ነገር ፡ ግን ፡ እያደር ፡ ያብባል ፡ እያደር ፡ ይጥማል

የእግዚአብሄር ፡ ልጅ ፡ ሁሌ ፡ አሸናፊ
የጠላቱን ፡ ድፍረት ፡ ገፋፊ
በዙፋን ፡ ላይ ፡ ሁሌ ፡ የሚኖረው
ኢየሱስ ፡ ጌታ ፡ ነው

አዝ:- ሰማይ ፡ ዙፋኑ ፡ መቀመጫው
ምድርም ፡ ለእግሮቹ ፡ መረገጫ
ስሙ ፡ ምንጊዜም ፡ የሚረታ
ትላንትም ፡ ዛሬም ፡ ነገም ፡ ጌታ
የእኔ ፡ መድህን ፡ ጌታ (፪x)