ይመስገን ፡ ጌታ (Yimesgen Geta) - አዲስ ፡ አበባ ፡ መካነ ፡ ኢየሱስ ፡ ለ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲስ ፡ አበባ ፡ መካነ ፡ ኢየሱስ ፡ ለ ፡ መዘምራን
(Addis Ababa Mekane Yesus Choir Le)

Addis Ababa Mekane Yesus Choir Le 1.jpg


(1)

እንዳንተ ያለ የለም
(Endante Yale Yelem)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፹ ፯ (1994)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲስ ፡ አበባ ፡ መካነ ፡ ኢየሱስ ፡ ለ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Addis Ababa Mekane Yesus Choir Le)

ይመስገን ጌታ ይመስገን
ይመስገን ኢየሱስ ይመስገን
ይመስገን ጌታ ይመስገን
ይመስገን ኢየሱስ ይመስገን
ይመስገን ከአሁን እስከ ዘላለም

በሰማያዊ በረከት ባረከን
በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለብን ሆንን
በክርስቶስ ለእርሱ ተመረጥን
የእርሱ ልጆች አንድንሆን
አስቀድሞ ወሰነን
ይመስገን እንላለን

ይመስገን ጌታ ይመስገን
ይመስገን ኢየሱስ ይመስገን
ይመስገን ጌታ ይመስገን
ይመስገን ኢየሱስ ይመስገን
ይመስገን ከአሁን እስከ ዘላለም

በደሙ የተዋጀን ልጆቹ ሆነናል
በጌታችን በኢየሱስ ለዘላለም ከብረናል
የፈቃዱን ሚሥጢር ለኛ አስታውቆናል
ክቡር በሆነው መንፈሱ
በእውነቱ አትሞናል
ይክበርልን ብለናል

ይመስገን ጌታ ይመስገን
ይመስገን ኢየሱስ ይመስገን
ይመስገን ጌታ ይመስገን
ይመስገን ኢየሱስ ይመስገን
ይመስገን ከአሁን እስከ ዘላለም

በጌታ ደስታ አክሊል ተሰጥቶናል
ምህረት ርህራሄ በርሱ ተሞልተናል
መልካም ስራ በኛ ለማድረግ ፈጥሮናል
በዙፋኑ አስቀምጦናል
ለዘላለም ከብረናል
እኛም ይክበር ብለናል

ይመስገን ጌታ ይመስገን
ይመስገን ኢየሱስ ይመስገን
ይመስገን ጌታ ይመስገን
ይመስገን ኢየሱስ ይመስገን
ይመስገን ከአሁን እስከ ዘላለም