መለጠፊያ:Alb

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝማች እግዚአብሄር እያለ ለምን እፈራለሁ/እሰጋለሁ አምናንም አቻምናንም ክንዱን/እጁን አይቻለሁ አምናንም አቻምናንም በድል አልፌያለሁ


ሸለቆው ተራራው ከፍታው አቤት ከእርሱ ጋራ ከፊት ከፊት ሲሄድ እጄን ይዞ እኔን እየመራ አይቼዋለሁ ጥበቃውን ምህረቱን ለልጁ እንዳበዛ ዛሬም ቢሆን አምነዋለሁ አይተወኝም አንዲሁ እንደዋዛ


አዝማች

ክእናት ቤት ከአባቱ ከዘመዱ አብርሃምን ብቻውን ጠራና እኔ ወደማሳይህ አገር ሂድ ብሎ አዘዘውና ቃልኪዳን ገባለት ሊባርከው ለዘሩ ምድርን ሊያወርሰው እንደተናገረው የብዙ ህዝብ አባት አደረገው

አዝማች

በቃሉ ተናግሮኝ ጠብቄው በጸሎቴ ምንም አልነሳኝም አባት አለኝ ብዬ ተመክቼ አላሳፈረኝም በፍጹም አልሰጋም ተደላደልኩ በአባቴ ቤት እግሬ ተተከለ ነገም ለሚመጣው አልፈራም አማኑኤል አለ