Tesfaye Gabisso/Yenazretu Eyesus/Egziabhier Sireda

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
በሕይወት ጐዳና ፈተና ቢበዛም 
ጌታን እየጠራ ንጹህ ሰው አይጠፋም 
እጄን ያዘኝ ብሎ ሲጮህ  ይሰማዋል 
ከረግረግ አውጥቶ በድል ይመራዋል

አዝ፦ እግዚአብሔር ሲረዳ ከሰማያት ወርዶ በደልን ሲያስወግድ በቅንነት ፈርዶ አላያችሁም ወይ ወጥመዱ ሲሰበር ምርኮኛው ተለቆ ማዳኑን ሲናገር

ችግረኛውን ሊውጥ ጠላት ሲገዳደር በሚያስፈራራ ቃል በትዕቢት ሲናገር ደርሶ የሚታደግ እግዚአብሔር ብቻ ነው በሰው መታመን ግን የከንቱ ከንቱ ነው

አዝ፦ እግዚአብሔር ሲረዳ ከሰማያት ወርዶ በደልን ሲያስወግድ በቅንነት ፈርዶ አላያችሁም ወይ ወጥመዱ ሲሰበር ምርኮኛው ተለቆ ማዳኑን ሲናገር

ያለውን ተነጥቆ ሁሉን ነገር አጥቶ ከአጠገቡ የሚቆም ጌታ ብቻ ቀርቶ በእንግድነት አገር ተገፍቶ ለሚያልፈው ተስፋው መሰረቱ አምላኩ ብቻ ነው

አዝ፦ እግዚአብሔር ሲረዳ ከሰማያት ወርዶ በደልን ሲያስወግድ በቅንነት ፈርዶ አላያችሁም ወይ ወጥመዱ ሲሰበር ምርኮኛው ተለቆ ማዳኑን ሲናገር

የቅዱሳን ረድኤት ከሰማይ ይመጣል ዘመናትን ቆጥሮ ጌታ ይመለሳል የልጆቹን እንባ ከዓይናቸው ያብሳል ክብርና ምሥጋና ለሥሙ ይሆናል

አዝ፦ እግዚአብሔር ሲረዳ ከሰማያት ወርዶ በደልን ሲያስወግድ በቅንነት ፈርዶ አላያችሁም ወይ ወጥመዱ ሲሰበር ምርኮኛው ተለቆ ማዳኑን ሲናገር