Dereje Kebede/Adagnie Yesus/Ahadu Elalehugn

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አሃዱ እላለሁ በምስጋና
አፌን እክፍታለሁ በምስጋና
እርሱ ያሰበልኝ በለጠና
የእኔ ከንቱ ሆኖ ቀርቷልና

ወጥቼ ወርጄ ብዙ አስቤአለሁ አውጠንጥኛለሁ
ልቤ እሰክሚጨነቅ በስጋ ጉዞ ተክለፍልፌአለሁ
ኋላ ግን በየሱስ ተሰብስቤያለሁ /፪

ፈቃዱን አውቄ በምስጋና ቃል ስሙን ጠርቼ
እውነተኛ ድምፁን ከአንደበቱ ጠርቶኝ ስምቼ
እርሱን እጠብቃለሁ ሌላውን ትቼ /፪

በከንቱ ነበረ መደካከሜ ላይ ታች ማለቴ
ነገ ዛሬ እንዲሆን በምኞት ሩጫ እጅግ መትጋቴ
አሁን ግን ልቀበል ከላይ ካባቴ /፪

እንግዲህ ካገኘሁ አጋዥ ከአርያም ሐሳቤን ጠቅላይ
ደቂቃም አታልፍም አይኔን አንስቼ ወደላይ ሳላይ
ድል ይላክልኛል ከሩቅ ከሰማይ /፪