ፀጋው ፡ ነው (Tsegaw New) - በረከት ፡ ተስፋዬ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
በረከት ፡ ተስፋዬ
(Bereket Tesfaye)

Bereket Tesfaye 1.jpeg


(1)

ሊቀ ፡ ካህኔ
(Liqe Kahenie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ (2007)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 5:50
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የበረከት ፡ ተስፋዬ ፡ አልበሞች
(Albums by Bereket Tesfaye)

 
አዝ:- ፀጋው ፡ ነው ፡ እኔን ፡ የሚያቆመኝ
ምህረቱ ፡ ነው ፡ እንዲህ ፡ የሚያዘምረኝ (፪x)

ሁልጊዜ ፡ ችኩል ፡ ነው ፡ ሲያዩት ፡ ደፋር ፡ መሳይ
ዶሮ ፡ ሳይጮህ ፡ በፊት ፡ ሶስት ፡ ጊዜ ፡ ክህዶታል
በሰው ፡ አይን ፡ ቢሆን ፡ ይህ ፡ ሰው ፡ ከሀዲ ፡ ነው
የፀጋው ፡ ጉልበት ፡ ግን ፡ ዳግም ፡ ሰው ፡ አረገው

አዝ:- ፀጋው ፡ ነው ፡ እኔን ፡ የሚያቆመኝ
ምህረቱ ፡ ነው ፡ እንዲህ ፡ የሚያዘምረኝ (፪x)

ቢሆንማ ፡ ኑሮ ፡ በክብር ፡ በዝና
በገንዘብም ፡ ብዛት ፡ ብዙ ፡ ብልጥግና
እንዴት ፡ እሆን ፡ ነበር ፡ እርቆኝ ፡ መዳኔ
ግን ፡ እንዲያው ፡ ወደደኝ ፡ አሰበኝ ፡ መድህኔ
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ጌታዬ ፡ ልዩ ፡ ነው
የተረሳውን ፡ ሰው ፡ እንዲህ ፡ ሚያስታውሰው

አዝ:- ፀጋው ፡ ነው ፡ እኔን ፡ የሚያቆመኝ
ምህረቱ ፡ ነው ፡ እንዲህ ፡ የሚያዘምረኝ (፪x)

በማይመስል ፡ ነገር ፡ መስራት ፡ የሚችል
የአለምንም ፡ ጥበብ ፡ በኔ ፡ ሚያሳፍር
ልጁንም ፡ ገለጠው ፡ በእኔው ፡ ሁኔታ
እኔን ፡ ውዳቂውን ፡ አከበረ ፡ ጌታ

አዝ:- ፀጋው ፡ ነው ፡ እኔን ፡ የሚያቆመኝ
ምህረቱ ፡ ነው ፡ እንዲህ ፡ የሚያዘምረኝ (፪x)

በራሴ ፡ አልቆምኩም ፡ ሚስጥሩ ፡ ገብቶኛል
ጸጋን ፡ አትረፍርፎ ፡ እየሱስ ፡ ሰጥቶኛል
ከቶ ፡ ዝም ፡ አልልም ፡ አዜምለታለሁ
ላከበረኝ ፡ ጌታ ፡ ክብር ፡ እሰጣለሁ
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ጌታዬ ፡ ልዩ ፡ ነው
የተረሳውን ፡ ሰው ፡ እንዲህ ፡ ሚያስታውሰው

አዝ:- ፀጋው ፡ ነው ፡ እኔን ፡ የሚያቆመኝ
ምህረቱ ፡ ነው ፡ እንዲህ ፡ የሚያዘምረኝ (፪x)