ላድንቅህ (Ladenekeh) - ዮሐንስ ፡ በላይ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዮሐንስ ፡ በላይ
(Yohannes Belay)

Lyrics.jpg


(4)

ላድንቅህ
(Ladenekeh)

ዓ.ም. (Year): 2018
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዮሐንስ ፡ በላይ ፡ አልበሞች
(Albums by Yohannes Belay)

የነፍሴ ፡ ቋንቋ ፡ ነህ ፡ (የሕይወቴ ፡ ዜና) ፪X
ማወደስ ፡ የማደንቅ ፡ (የአንተን ፡ ልእልና)፪X ፡
የእኔ ፡ ተልእኮ ፡ ነው ፡ ጥሪና ፡ ውሳኔ
እስትንፋሴ ፡ እስካለች ፡ ቀሪውን ፡ ዘመኔ

ኢየሱስ ፡ ላድንቅህ ፬X

በፏፏቴው ፡ ውበት ፡ (እጆችህ ፡ ባበጁት)፪X
በተፈጥሮ ፡ ቀለም ፡ (ሁሉን ፡ ባቆነጁት)፪X
ግርምቴም ፡ አይበቃ ፡ (ዝም ፡ አይልም ፡ አፌ)፪X
ምሥጋና ፡ ይፈልቃል ፡ (ከመስክ ፡ ከደጃፌ)፪X

የተፈጠርኩበት ፡ የምድር ፡ ላይ ፡ ኑሮ
የተፃፈልኝም ፡ ሁሉም ፡ ተቀምሮ
አንተን ፡ ማወደስ ፡ ነው ፡ ክበር ፡ ክበር ፡ ማለት
ጅማረው ፡ ፊፃሜ ፡ (የሕይወቴ ፡ መሠረት)፪X

የነፍሴ ፡ ቋንቋ ፡ ነህ ፡ (የሕይወቴ ፡ ዜና) ፪X
ማወደስ ፡ የማደንቅ ፡ (የአንተን ፡ ልእልና)፪X ፡
የእኔ ፡ ተልእኮ ፡ ነው ፡ ጥሪና ፡ ውሳኔ
እስትንፋሴ ፡ እስካለች ፡ ቀሪውን ፡ ዘመኔ
 
ኢየሱስ ፡ ላድንቅህ ፬X

የሰማዩ ፡ ቀለም ፡ (የአድማሳቱ ፡ ግርማ)፪X
የንፋሱ ፡ ፉጨት ፡ (የአዋፋቱ ፡ ዜማ) ፡ ፪X
ክብርህን ፡ መናገር ፡ (ውዳሴን ፡ ማሳረግ)፪X
ዝናህን ፡ መተረክ ፡(ከፍ ፡ ከፍ ፡ ማድረግ)፪X

የተፈጠርኩበት ፡ የምድር ፡ ላይ ፡ ኑሮ
የተፃፈልኝም ፡ ሁሉም ፡ ተቀምሮ
አንተን ፡ ማወደስ ፡ ነው ፡ ክበር ፡ ክበር ፡ ማለት
ጅማረው ፡ ፊፃሜ ፡ (የሕይወቴ ፡ መሠረት)፪X