የአባትነቱን (Yeabatenetun) - መዝሙረ ፡ ደረጀ

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
መዝሙረ ፡ ደረጀ
(Mezmure Dereje)

Mezmure Dereje 3.jpg


(3)

ጻዲቅ ሆይ በርታ
(Tsadeq Hoy Berta)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2012)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 5:36
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመዝሙረ ፡ ደረጀ ፡ አልበሞች
(Albums by Mezmure Dereje)

አዝ፥ ክብር ፡ ክብር ፡ ይሁንለት(4)
ክብር ፡ ክብር ፡ የአባትነቱን
ክብር ፡ ክብር ፡ የጌትነቱን
አምጡለት ፡ ክብር ፡ የሚገባውን(2)

ልጅም ፡ አባቱን ፡ ባሪያም ፡ ጌታውን
እንደሚያከብር ፡ አምጡለት ፡ ክብሩን
ጤነኛ ፡ የሆነ ፡ ጠቦት ፡ አምጡለት
የሚገባውን ፡ ፊቱ ፡ ሰዉለት

አዝ፥ ክብር ፡ ክብር ፡ ይሁንለት(4)
ክብር ፡ ክብር ፡ የአባትነቱን
ክብር ፡ ክብር ፡ የጌትነቱን
አምጡለት ፡ ክብር ፡ የሚገባውን(2)

ለአባትነትህ ፡ የሚገባህን
ቤትህ ፡ አትጣው ፡ መፈራትህን
ልጆችህ ፡ ያክብሩህ ፡ ይስሙ ፡ ቃልህን
አንተን ፡ የሚፈሩ/የሚወዱ ፡ ይሙሉት ፡ ቤትህን

የበኩር ይሁን የመጀመሪያው
ለአንተ ፡ የሚሰጠው ፡ ለአንተ ፡ የሚሰዋው
ንጹህ ፡ ይሁንልህ ፡ እንደምትወደው
በፊትህ ፡ ተንኖ ፡ የምታሸተው

አዝ፥ ክብር ፡ ክብር ፡ ይሁንለት(4)
ክብር ፡ ክብር ፡ የአባትነቱን
ክብር ፡ ክብር ፡ የጌትነቱን
አምጡለት ፡ ክብር ፡ የሚገባውን(2)

ለአባትነትህ ፡ የሚገባህን
ቤትህ ፡ አትጣው ፡ መፈራትህን
ልጆችህ ፡ ያክብሩህ ፡ ይስሙ ፡ ቃልህን
አንተን ፡ የሚፈሩ/የሚወዱ ይሙሉት ፡ ቤትህን