ለሚጠሩህ ፡ ቅርብ (Lemiteruh Qerb) - ለምለም ፡ ንጋቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ለምለም ፡ ንጋቱ
(Lemlem Nigatu)

Lyrics.jpg


(Volume)

ለሚጠሩህ ፡ ቅርብ
(Lemiteruh Qerb)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፯ (2014)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለምለም ፡ ንጋቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Lemlem Nigatu)

እግዚአብሔርን ሊሰሙ ለሚወዱ ትናገራለህ
ሊያዩህ ለሚሹ ለናፈቁ ትገለጣለህ
በቀናዋ መንገድ ሊሄዱ ለመረጡ
እስከ ፍጻሜው ትመራቸዋለህ

አዝ፦
ለሚጠሩህ ቅርብ ለሚጠሩህ ቅርብ
ለሚፈልጉህ ጌታ ትገኛለህ
ለሚጠሩህ አሁን ለሚጠሩህ ዛሬም
ለሚፈልጉህ ፈጥነህ ትገኛለህ


ከመቼውም ይልቅ አንተን እፈልጋለሁ
ሁሌ ወዳንተ ልጠጋ ወዳለሁ
ፍቅርህ ሰርጾ ውስጤ ገብቷል
ሌላው ነገር በፊቴ ቀልሎብኛል
ፍቅርህ ሰርጾ ውስጤ ገብቷል
ሌላው ነገር በፊቴ ቀልሎብኛል

በእውነትና በመንፈስ ለሚፈልጉህ
ሁሉን ነገር ትተው ለተከተሉህ
እንደ ቃልህ አንተ ትገኛለህ
ተዓምራትን በእነርሱ ታደርጋለህ
እንደ ቃልህ አንተ ትገኛለህ
ተዓምራትን በእነርሱ ታደርጋለህ

አዝ፦
ለሚጠሩህ ቅርብ ለሚጠሩህ ቅርብ
ለሚፈልጉህ ጌታ ትገኛለህ
ለሚጠሩህ አሁን ለሚጠሩህ ዛሬም
ለሚፈልጉህ ፈጥነህ ትገኛለህ


ቀድሞ ለአባቶቼ እንዳረክላቸው
በትውልድ መካከል እንዳከበርካቸው
ዛሬም በእኛ ዘመን ቅርብ ነህ
ማዳንህን አያለሁ ትሰራለህ
ዛሬም በእኛ ዘመን ቅርብ ነህ
ክንድህን አያለሁ ትሰራለህ

አዝ፦
ለሚጠሩህ ቅርብ ለሚጠሩህ ቅርብ
ለሚፈልጉህ ጌታ ትገኛለህ
ለሚጠሩህ አሁን ለሚጠሩህ ዛሬም
ለሚፈልጉህ ፈጥነህ ትገኛለህ