የናርዶስ ፡ ሽቶዬ (Yenardos Shetoyie) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ለዓለም ፡ ጥላሁን
(Lealem Tilahun)

Lealem Tilahun 3.jpg


(3)

የናርዶስ ፡ ሽቶዬ
(Yenardos Shetoyie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2014)
ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 6:19
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለዓለም ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Lealem Tilahun)

የናርዶስ ፡ ሽቶዬ ፡ የአልባስጥሮስ
መጓደጃዬ ፡ ውድ ፡ ኢየሱስ
ልቤ ፡ ከልብህ ፡ ጋር ፡ ተቆራኝቶ
መኖር ፡ ወደደ ፡ አንተን ፡ አግኝቶ (፪x)

አንተን ፡ አግኝቶ (፬x)

አዝ፦ ቅዱሱ ፡ እግዚአብሔር ፡ የማውቀህ ፡ ከልጅነቴ
ንጉሡ ፡ እግዚአብሔር ፡ የምሻህ ፡ ከልጅነቴ
እርስቴም ፡ ተድላዬም ፡ ጥጋቤም
አንተ ፡ ነህ ፡ ማር ፡ እና ፡ ወተቴ (፭x)

የቆላ ፡ አበባ ፡ ፅጌረዳዬ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ ውሎ ፡ መግቢያዬ
በማሰማሪያህ ፡ በታዛ ፡ ሥር
አንተን ፡ ሳመልክህ ፡ ውዬ ፡ ልደር (፭x)

ውዬ ፡ ልደር (፬x)

መጣሁኝ ፡ ወዳሳየኸኝ ፡ ውብ ፡ ሥፍራ
አየሁ ፡ የግርማህን ፡ ፀዳል ፡ ሲያበራ
ወዳጄ ፡ ለመሆኑ ፡ ሰው ፡ አወቀህ ፡ ወይ
ቁንጅናህ ፡ ለሀገር ፡ የሚተርፍ ፡ አይደል ፡ ወይ (፫x)

አዝ፦ ቅዱሱ ፡ እግዚአብሔር ፡ የማውቀህ ፡ ከልጅነቴ
ንጉሡ ፡ እግዚአብሔር ፡ የምሻህ ፡ ከልጅነቴ
እርስቴም ፡ ተድላዬም ፡ ጥጋቤም
አንተ ፡ ነህ ፡ ማር ፡ እና ፡ ወተቴ (፭x)

ልቤ ፡ መልካምን ፡ ቅኔ ፡ አፈለቀ
ንጉሡን ፡ ጌታ ፡ እያደነቀ
ውበቱ ፡ ከአምራል ፡ ከሰው ፡ ይልቅ
የእኔማ ፡ ኢየሱስ ፡ ከብርቅም ፡ ብርቅ (፬x)

አዝ፦ ቅዱሱ ፡ እግዚአብሔር ፡ የማውቀህ ፡ ከልጅነቴ
ንጉሡ ፡ እግዚአብሔር ፡ የምሻህ ፡ ከልጅነቴ
እርስቴም ፡ ተድላዬም ፡ ጥጋቤም
አንተ ፡ ነህ ፡ ማር ፡ እና ፡ ወተቴ (፱x)