በቂ ነህ (Beqi Neh) - ሐረር አማኑኤል መንፈሳዊ ማህበር

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
ሐረር አማኑኤል መንፈሳዊ ማህበር
(Harar Amanuel Menfesawi Maheber)

Lyrics.jpg


(2)

አልበም
(beki neh)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፬ (2002)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 4:52
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሐረር አማኑኤል መንፈሳዊ ማህበር ፡ አልበሞች
(Albums by Harar Amanuel Menfesawi Maheber)

“እግዚአብሔር በቂ ነህ”
በሐረር አማኑኤል ኅብረት ኳዬር

(እግዚአብሔር) 2
(በቂ ነህ ከበቂም በላይ) 2 በቂ ነህ
ምን ጎሎብህ ምን አጥተህ
ሁሌ ሙሉ አይጎልህ
(ሁሉ በእጅህ ነው በደጅህ) 2

ስጦታህ ብዙ ነው ማንም አይመስልህም
ሁሌ ትሰጣለህ ከቶ አይጎልህም
ሰረገላዎችህ የብዙ ሺህ ናቸው
እጅህ ሰፊ ጌታ ሥራህ እጅግ ድንቅ ነው
ተትረፍርፈህ ጌታ ታትረፈርፋለህ
ሁሉ ያንተ የሆንህ (የሁሉ አምላክ ነህ) 2

(እግዚአብሔር) 2 ……

አለሁ የሚል ከቶ በችግር የሚደርስ
በመከራ ፈንታ ደስታን የሚክስ
ሊረዳ የሚተጋ ወገብ አሸንፍጦ
ሁሌ የሚያሰማራ እጅጉን አስፍቶ
ሁሉ በጠፋበት አንተ ብቻ አለህ
ጌታዬ ግን በቂ (ከበቂም በላይ ነህ) 2

(እግዚአብሔር) 2 ……

ሁሉ ከእጅ ጠፍቶ የሚያዝ ባይኖርም
ዙሪያ ገባው ባዶ ጨለማ ቢሆንም
እርሻ መብልን ባይሰጥ ከብቶችም ባይኖሩ
ወይንና በለስም ፍሬ ባያፈሩ
አንተ ግን ብቻህን ታደላድላለህ
በቂ ነህ ጌታዬ (ሃሳብ ታስጥላለህ) 2

(እግዚአብሔር) 2 ……