ንጉሥ ፡ ለወደደው (Negus Lewededew) - ሀና ፡ አላዩ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሀና ፡ አላዩ
(Hannah Alayou)


(1)

ንጉሥ ፡ ለወደደው
(Negus Lewededew)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፰ (2016)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 4:54
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሀና ፡ አላዩ ፡ አልበሞች
(Albums by Hannah Alayou)

ንጉሥ ፡ ስለወደደው ፡ እንዲህ ፡ ይደረግለታል
ንጉሥ ፡ ስላፈቀረው ፡ እንዲህ ፡ ይደረግለታል
ንጉሥ ፡ ስለወደደው ፡ ዘንጉ ፡ ይዘረጋለታል
ንጉሥ ፡ ስላፈቀረው ፡ ካባ ፡ ይደረብለታል (፪x)

እኔን ፡ ስለወደደኝ ፡ ኢየሱስን ፡ ሰጠኝ
እኔን ፡ ስላፈቀረኝ ፡ መድኃኒትን ፡ ሰጠኝ
እኔን ፡ ስለወደደኝ ፡ አንድ ፡ ልጁን ፡ ሰጠኝ
እኔን ፡ ስላፈቀረኝ ፡ አማኑኤልን ፡ ሰጠኝ

ንጉሥ ፡ ስለወደደኝ ፡ እኔስ ፡ ዕድለኛ ፡ ነኝ
ንጉሥ ፡ ስላከበረኝ ፡ እኔስ ፡ ዕድለኛ ፡ ነኝ

ለእኔ ፡ የተደረገው ፡ ብዙ ፡ እኮ ፡ ነው
ለእኔ ፡ የተሰራው ፡ ብዙ ፡ እኮ ፡ ነው
አንድ ፡ በአንድ ፡ እቆጥራለሁ
የእርሱን ፡ መልካምነት ፡ እናገረዋለሁ (፪x)

ምን ፡ ያልተደረገ ፡ ያልሆነልኝ ፡ አለ
ከኢየሱስ ፡ ጀምሮ ፡ ለእኔ ፡ ያልተሰጠ
ከመልካምነቱ ፡ እኔን ፡ አጠገበ
ንጉሥ ፡ እኔን ፡ ወዶ ፡ እንዲህ ፡ አደረገ

ለእኔ ፡ የተደረገው ፡ ብዙ ፡ እኮ ፡ ነው
ለእኔ ፡ የተሰራው ፡ ብዙ ፡ እኮ ፡ ነው
አንድ ፡ በአንድ ፡ እቆጥራለሁ
የእርሱን ፡ መልካምነት ፡ እናገረዋለሁ (፪x)

አክሊል ፡ እንደለበሰ ፡ ያጌጠ ፡ ሙሽራ
ሕይወቴ ፡ በደሙ ፡ ታጥባ ፡ አምራ
በፊቱ ፡ የመግባትን ፡ ድፍረት ፡ አግኝታለች
ለልዑል ፡ እግዚአብሔር ፡ ዛሬ ፡ ታዜምለታለች

ቸር ፡ ነው (፪x)
ምሕረቱ ፡ ብዙ ፡ ነው
ፍቅሩ ፡ የማያልቅ ፡ ነው (፪x)

ወደደኝ ፡ አዳነኝ
ለክብሩ ፡ እኔን ፡ መረጠኝ (፪x)

(ወደደኝ ፡ አዳነኝ
ለክብሩ ፡ እኔን ፡ መረጠኝ (፪x))