ሀብተ ፡ ሰማይ (Habte Semay) - ሀና ፡ ተ ክሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሀና ፡ ተ ክሌ
(Hana Tekle)

Hana Tekle 3.jpg


(3)

ሀብተ ፡ ሰማይ
(Habte Semay)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ ፫ (2020)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሀና ፡ ተ

ክሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Hana Tekle)

አዲስ ፡ ሰማይ ፡ አዲስ ፡ ምድር
የብርሃን ፡ ሀገር ፡ የብርሃን ፡ ቅጥር
ምርአፍ ፡ ተዘግቶ ፡ ምርአፍ ፡ ሲጀመር
አየዋለው ፡ ያኔ ፡ በድል ፡ በክብር

ሲያልፍ ፡ ፊተኛው ፡ ሰማይ
ደግሞ ፡ አንደገና ፡ አዲስ ፡ ሰማይ
ሲያበቃ ፡ ይሄኛው ፡ ምድር
ዘለዓለም ፡ አለ ፡ የክብር ፡ ምድር (፪x)

ጨለማ ፡ ዳግም ፡ በማይሰፍነበት
ፀሐይም ፡ ጨረቃም ፡ በሌሉበት
በጉ ፡ ብርሃን ፡ ነዉ ፡ ያበራል
ሀገር ፡ በክርስቶስ ፡ ይደምቃል

አዝ፦ ሀብተ ፡ ሰማይ ፡ ፅኑ ፡ ተስፋዬ
ከአየሱስ ፡ ጋር ፡ ለዘላለም ፡ መኖርያዬ
ሀብተ ፡ ሰማይ ፡ ፅኑ ፡ ተስፋዬ
ከአየሱስ ፡ ጋር ፡ ለዘላለም ፡ መንገሻዬ

አይን ፡ ያላየው ፡ ጆሮም ፡ ያልሰማው
ጌታ ፡ ለሚወዱት ፡ ያዘጋጀው
ልብሳቸውን ፡ በበጉ ፡ ደም ፡ ላጠቡ
የሰፋውን ፡ መንገድ ፡ ጥለው ፡ ለዘለቁ

አዝ፦ ሀብተ ፡ ሰማይ ፡ ፅኑ ፡ ተስፋዬ
ከአየሱስ ፡ ጋር ፡ ለዘላለም ፡ መኖርያዬ
ሀብተ ፡ ሰማይ ፡ ፅኑ ፡ ተስፋዬ
ከአየሱስ ፡ ጋር ፡ ለዘላለም ፡ መንገሻዬ

በተስፋ ፡ ድንበር ፡ በፍቅር ፡ ሀገር
የእምነት ፡ ፅናት ፡ ምላሽ ፡ ሲሰምር
ሲበሰር ፡ የዘለዓለሙ ፡ ደስታ
የታመኑት ፡ የናፈቁት ፡ ላይም ፡ ሲበቃ

አዝ፦ ሀብተ ፡ ሰማይ ፡ ፅኑ ፡ ተስፋዬ
ከአየሱስ ፡ ጋር ፡ ለዘላለም ፡ መኖርያዬ
ሀብተ ፡ ሰማይ ፡ ፅኑ ፡ ተስፋዬ
ከአየሱስ ፡ ጋር ፡ ለዘላለም ፡ መንገሻዬ

ሌት ፡ በማያውቀው ፡ የቀን ፡ ጅረት
ብርሃን ፡ ውሎ ፡ ብርሃን ፡ ማደር
ምናለ ፡ ደስታ ፡ ምናለ ፡ ውበት
ከክርስቶስ ፡ ጋር ፡ ነግሶ ፡ አንደማየት

ሞት ፡ በማይገጥመው ፡ የህይወት ፡ ጅረት
ድል ፡ ከነሱት ፡ ጋር ፡ ተካፍሎ ፡ እርስት
ምናለ ፡ ውበት ፡ ምናለ ፡ ፍሰሃ
አንደመገኘት ፡ ከዚህ ፡ ክብር ፡ ጋር

ሲያልፍ ፡ ፊተኛው ፡ ሰማይ
ደግሞ ፡ አንደገና ፡ አዲስ ፡ ሰማይ
ሲያበቃ ፡ ይሄኛው ፡ ምድር
ዘላለም ፡ አለ ፡ የክብር ፡ ምድር