አጠገቤ ፡ ሆኗል (Ategebie Honual) - ሐብታሙ ፡ ኩመላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሐብታሙ ፡ ኩመላ
(Habtamu Kumela)


(1)

አጠገቤ ፡ ሆኗል
(Ategebie Honual)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሐብታሙ ፡ ኩመላ ፡ አልበሞች
(Albums by Habtamu Kumela)

አዝአጠገቤ ፡ ሆኗል ፡ ጌታ (፬x)
ከእንግዲህ ፡ የቱ ፡ ያስፈራኛል
እግዚአብሔር ፡ ጋሻ ፡ ሆኖልኛል
ከእንግዲህ ፡ የቱ ፡ ያሰጋኛል
አባቴ ፡ ቅጥር ፡ ሆኖልኛል

በብቸኝነቴ ፡ አይዞህ ፡ ባይ ፡ ማጣቴ
ትዝ ፡ ሲለኝ (፪x)
የለቅሶ ፡ እንጉርጉሮ ፡ ሲሰማ ፡ ከቤቴ
ትዝ ፡ ሲለኝ (፪x)

የእኔስ ፡ ነገር ፡ የእኔስ
በዓይን ፡ አይቶ ፡ ሳለቅስ
ያልራቀኝ ፡ ንጉሥ
የልጅነት ፡ ጓደኛ
ስሆን ፡ ያኔ ፡ ብቸኛ
ኢየሱስ ፡ አለኛ

አዝአጠገቤ ፡ ሆኗል ፡ ጌታ (፬x)
ከእንግዲህ ፡ የቱ ፡ ያስፈራኛል
እግዚአብሔር ፡ ጋሻ ፡ ሆኖልኛል
ከእንግዲህ ፡ የቱ ፡ ያሰጋኛል
አባቴ ፡ ቅጥር ፡ ሆኖልኛል

የቅርብ ፡ ወንድሞቼ ፡ ሁሉ ፡ የከዱኝ
ትዝ ፡ ሲለኝ (፪x)
ያለርህራሄ ፡ ጉድጓድ ፡ የጣሉኝ
ትዝ ፡ ሲለኝ (፪x)

የእኔስ ፡ ነገር ፡ የእኔስ
በዓይን ፡ አይቶ ፡ ሳለቅስ
ያልራቀኝ ፡ ንጉሥ
የልጅነት ፡ ጓደኛ
ስሆን ፡ ያኔ ፡ ብቸኛ
ኢየሱስ ፡ አለኛ

አዝአጠገቤ ፡ ሆኗል ፡ ጌታ (፬x)
ከእንግዲህ ፡ የቱ ፡ ያስፈራኛል
እግዚአብሔር ፡ ጋሻ ፡ ሆኖልኛል
ከእንግዲህ ፡ የቱ ፡ ያሰጋኛል
አባቴ ፡ ቅጥር ፡ ሆኖልኛል

ለእኔስ ፡ አይዞህ ፡ ብለው ፡ የሚያጽናኑኝ
ወዳጆቼም ፡ ችላ ፡ ቢሉኝ
የቅርቦቼም ፡ ችላ ፡ ቢሉኝ
እናት ፡ ልጇን ፡ እንኳን ፡ ብትረሳ
ልጄ ፡ ካለ ፡ የማይከዳ
ጌታ ፡ አለ ፡ ከእኔስ ፡ ጋራ (፪x)