From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
ዳዊት ጌታቸው (Dawit Getachew)
|
|
፪ (2)
|
አልበም (Amnihalehu)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፳ ፻ ፲ ፬ (2021)
|
ቁጥር (Track):
|
፲ (10)
|
ርዝመት (Len.):
|
5:14
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የዳዊት ጌታቸው ፡ አልበሞች (Albums by Dawit Getachew)
|
|
ሁሉን ፡ የምትችል ፡ የአብርሃም ፡ አምላክ
ስለ ፡ ተስፋ ፡ ቃልህ ፡ ቅዱስ ፡ ስምህ ፡ ይባረክ
በእምነት ፡ በመጽናት ፡ ክብርህን ፡ ሰጥሃለው
አልጠራጠርም ፡ ቃልህን ፡ አምናለው
አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ አምንሃለው
ከማየው ፡ በላይ ፡ ቃልህን ፡ አምናለው
በምንም ፡ አይነት ፡ እንደማተወኝ
የከፈልክብኝ ፡ እየሱስ ፡ አሳየኝ
እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ አምንሃለው
ከራሴ ፡ በላይ ፡ ቃልህን ፡ አምናለው
በዙፋንህ ፡ ላይ ፡ እንደምትኖር ፡ ፀንትህ
ለሚወዱህም ፡ ዋጋን ፡ እየሰጠህ
ከጠየኩህ ፡ እና ፡ ከማስበው ፡ በላይ
ማድረግ ፡ ለሚቻልህ ፡ ያለ ፡ አንዳች ፡ ከልካይ
ተስፋን ፡ በሚያስቆርጥ ፡ ባለቀ ፡ ነገር ፡ ላይ
ህይወት ፡ የምትዘራ ፡ አንተ ፡ አደለህም ፡ ወይ
አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ አምንሃለው
ከማየው ፡ በላይ ፡ ቃልህን ፡ አምናለው
በምንም ፡ አይነት ፡ እንደማተወኝ
የከፈልክብኝ ፡ እየሱስ ፡ አሳየኝ
እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ አምንሃለው
ከራሴ ፡ በላይ ፡ ቃልህን ፡ ይዣለው
በዙፋንህ ፡ ላይ ፡ እንደምትኖር ፡ ፀንትህ
ለሚወዱህም ፡ ዋጋን ፡ እየሰጠህ
በእምነት ፡ ጠብቃለው ፡ ቃልህን ፡ በተስፋ
የሚታይ ፡ ደመና ፡ ለጊዜው ፡ ቢጠፋ
ሃይሌ ፡ አንተ ፡ ነህና ፡ ፍጹም አልታክትም
በአንተ ፡ የታመኑትን ፡ ከቶ ፡ አትጥላችሀውም
ክንድህን ፡ ታምኜ ፡ ባንተ ፡ እመካለው
የነገርከኝን ፡ ተስፋ ፡ አደርጋለው
በቃልህ ፡ ታማኝ ፡ አምላክ ፡ ነህና
እጠብቅሃለው ፡ ሆኜ ፡ በምስጋና (፫X)
|