From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
|
|
ብዙ ፡ ሙሉጌታ (Bezu Mulugeta)
|
|
|
|
ልዩ ፡ እትም (Esp)
|
አልበም (፩)
|
| ቁጥር (Track):
|
፯ (7)
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
|
የብዙ ፡ ሙሉጌታ ፡ አልበሞች (Albums by Bezu Mulugeta)
|
|
|
አዝ፦ ብዙ ፡ ትቶልኛል ፡ ብዙ ፡ እወደዋለሁ
ብዙ ፡ እኔን ፡ ምሮኛል ፡ ብዙ ፡ አከብረዋለሁ
በብዙ ፡ ምሥጋና ፡ ፊቱ ፡ እቀርባለሁ
በብዙ ፡ ዝማሬ ፡ ጌታን ፡ አከብራለሁ
ገበናን ፡ ሰው ፡ መግለጥ ፡ ይወዳል
ኃጢአትን ፡ መቼ ፡ ይቅር ፡ ይላል
የእኔ ፡ ውድ ፡ ከዝህ ፡ ሁሉ ፡ ልዩ ፡ (፪×)
ችሎኛል ፡ ሰዎች ፡ ይህንን ፡ ስሙኙ ፡ (፪×)
አዝ፦
ስንቆም ፡ ሞገስ ፡ የሚያለብሰን
ጻድቃኖች ፡ አድርጐ ፡ የቆጠረን
ኢየሱስ ፡ ብዙ ፡ ትቶልናል ፡ (፪×)
ምሕረት ፡ ዛሬም ፡ ያኖረናል ፡ (፪×)
አዝ፦
ለመውገር ፡ ሁሉም ፡ ይቸኩላል
ድንጋዩን ፡ በእጁ ፡ ተሸሟል
ኢየሱስ ፡ የሰውን ፡ ድካም ፡ ያውቃል ፡ (፪×)
ከአመድ ፡ ላይ ፡ ምስኪኑን ፡ ያነሳል ፡ (፪×)
አዝ፦
ውለታው ፡ ለእኔ ፡ በዝቶብኛል
ነውሬን ፡ ኢየሱስ ፡ ወስዶልኛል
ውበቴ ፡ ድምቀቴ ፡ ሽቶዬ ፡ (፪×)
ጠረኔ ፡ ሆነልኝ ፡ ጌታዬ ፡ (፪×)
አዝ፦
ብዙ ፡ ትቶልኛል ፡ ብዙ ፡ እወደዋለሁ
ብዙ ፡ እኔን ፡ ምሮኛል ፡ ብዙ ፡ አከብረዋለሁ
በብዙ ፡ ምሥጋና ፡ ፊቱ ፡ እቀርባለሁ ፡ (፬×)
በብዙ ፡ ዝማሬ ፡ ጌታን ፡ አከብራለሁ ፡ (፬×)
|