አቤት ፡ አምላኬ (Abiet Amlakie) - ቤተልሔም ፡ ተዘራ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ተዘራ
(Bethlehem Tezera)

Bethlehem Tezera 1.jpg


(1)

አቤት ፡ አምላኬ
(Abiet Amlakie)

ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 5:31
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቤተልሔም ፡ ተዘራ ፡ አልበሞች
(Albums by Bethlehem Tezera)

አቤት ፡ አምላኬ ፡ ያደገልኝን ፡ ሳስተውለው ፡ ባረኩህ (፪x)
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ያደረክልኝ ፡ ሳስተውሰው ፡ ወደድኩህ (፪x)

ለካስ ፡ እንዲህ ፡ ነው (፫x)
ነፍሴን ፡ ያዳንካት ፡ ከጉድ ፡ ነው
ለካስ ፡ እንዲህ ፡ ነው (፫x)
ነፍሴን ፡ ያዳንካት ፡ ከሞት ፡ ነው (፪x)

የዘለዓለም ፡ ፍቅር ፡ የዘላለም ፡ ሕይወት
ይሄው ፡ አሰጥቶኛል ፡ ወደ ፡ አብ ፡ መግባት
ኢየሱስ ፡ አየሁት ፡ የፍቅርህን ፡ ልኩን
አኔ ፡ አስገዝቶኛል ፡ እስከ ፡ ሞት ፡ መሆኑ

ማንም ፡ ባያውቅህ ፡ የታወቅህ ፡ ነህ
ማንም ፡ ባያምንህ ፡ የታመንህ ፡ ነህ
እኔስ ፡ አውቄህ ፡ ሆንኩኝ ፡ ምስክር
ሳላመነታ ፡ ሳልደናገር (፪x)

እኔስ ፡ አውቄ ፡ ሆንኩኝ ፡ ምስክር
ሳላመነታ ፡ ሳልጠራጠር

ታሪክ ፡ ተረድቼ ፡ አይደለም ፡ ሲነገር ፡ ሰምቼ ፡ ብቻ ፡ አይደለም
የሰራህልኝን ፡ አስቤ ፡ እከተልሃለሁ ፡ ከልቤ
ታሪክ ፡ ተረድቼ ፡ አይደለም ፡ ሲነገር ፡ ሰምቼ ፡ ብቻ ፡ አይደለም
ያደረክልኝን ፡ አስቤ ፡ እኖርልሃለሁ ፡ ከልቤ

አውቄያለሁ ፡ አውቄያለሁ ፡ ተረድቻለሁ
የመኖሬ ፡ ትርጉም ፡ ሆኖ ፡ አግኝቼዋለሁ (፪x)

አቤቱ ፡ እንዳንተ ፡ ለኔ ፡ ማነው
ማንስ ፡ ነው ፡ ልሙትልሽ ፡ ያለው
 
ከሰማያት ፡ ወርደህ ፡ ያዳንከኝ ፡ አንተ
ለዘለዓለም ፡ ልገዛልህ ፡ ላንተ
ከሰማያት ፡ ወርደህ ፡ አድነህኛል
የሰራህልኝን ፡ ልቤ ፡ አውቆታል

ሳመልክህ ፡ በደስታ ፡ ሳከብርህ ፡ በደስታ
ለነፍሴ ፡ በሞት ፡ ፈንታ ፡ መዳን ፡ አውጀሃልና (፪x)

እንግዲህ ፡ ነፍሴን ፡ ካዳንክልኝማ
በደስታ ፡ እኖራለሁ ፡ በደስታ ፡ ላንተ ፡ ጌታ
በደስታ ፡ እኖራለሁ ፡ በደስታ

እንግዲህ ፡ ነፍሴን ፡ ካዳንክልኝማ
በውዴታ ፡ እገዛለሁ ፡ በውዴታ ፡ ላንተ ፡ ጌታ
በውዴታ ፡ እገዛለሁ ፡ በውዴታ