From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
በምድረበዳው(፪)
ጥሎ ፡ የማይሄድ ፡ ጌታ ፡ የሚያሳርፍ ፡ ነው
ከእናቴ ፡ ማህጸን ፡ ስላወቀኝ ፡ ጌታ
እንዳልጠፋ ፡ እንዳልሞት ፡ በብዙ ፡ ጥበቃ
እየጠበቀኝ ፡ እየደገፈኝ
እረኛዬ ፡ ሆኖ ፡ ጌታ ፡ አሳደገኝ
መሪዬ ፡ ነህ ፡ ለእኔ ፡ ብልህ ፡ ምን ፡ ያንስሃል ፡ ኢየሱሴ
ውበት ፡ ደምግባቴ ፡ ብልህ ፡ ምን ፡ ያንስሃል ፡ ኢየሱሴ(፪)
በመከራዬ ፡ ላይ ፡ ጋሻ ፡ የሆነኝ
ተስፋ ፡ በሌለበት ፡ ፍቅሩ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ እጄን ፡ የያዘኝ
ከማንም ፡ አብልጦ ፡ እኔን ፡ ሚጠጋጋ
(ኢየሱስ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ የእኔ ፡ ዋስ ፡ ጠበቃ)፪
የገረመኝ(፫) ፡ የጌታ ፡ ማዳን ፡ ለእኔ ፡ ገብቶኝ
የደነቀኝ(፪) ፡ የጌታ ፡ ፍቅር ፡ ለእኔ ፡ ገብቶኝ
እናገራለሁ ፡ አፌን ፡ ሞልቼ
??? ፡ በሮቼን
በምሥጋና(፫) ፡ ስሙን ፡ ላክብር ፡ እንደገና
በዕልልታ(፫) ፡ ዛሬም ፡ አለሁ ፡ በከፍታ
ክብሩን ፡ ትቶ ፡ ለእኔ ፡ ከሰማይ ፡ መጣልኝ
እዳዬን ፡ ከፈለ ፡ ከሲዖል ፡ አወጣኝ
ምን ፡ ልበል ፡ እንግዲህ ፡ ቃላቶች ፡ የሉኝም
የፍቅሩን ፡ ጥልቀት ፡ መግለጽ ፡ አልቻልኩኝም
የገረመኝ(፫) ፡ የጌታ ፡ ማዳን ፡ ለእኔ ፡ ገብቶኝ
የደነቀኝ(፪) ፡ የጌታ ፡ ፍቅር ፡ ለእኔ ፡ ገብቶኝ
እናገራለሁ ፡ አፌን ፡ ሞልቼ
??? ፡ በሮቼን
በምሥጋና(፫) ፡ ስሙን ፡ ላክብር ፡ እንደገና
በዕልልታ(፫) ፡ ዛሬም ፡ አለሁ ፡ በከፍታ
ማቄ ፡ ተቀደደ ፡ ዳግም ፡ ተወለድኩኝ
ልጅ ፡ የምሆንለት ፡ አባት ፡ አገኘሁኝ
ይኸው ፡ በተራዬ ፡ እመሰክራለሁ
ኢየሱስ ፡ ያድናል ፡ ብዬ ፡ አወራለሁ
የገረመኝ(፫) ፡ የጌታ ፡ ማዳን ፡ ለእኔ ፡ ገብቶኝ
የደነቀኝ(፪) ፡ የጌታ ፡ ፍቅር ፡ ለእኔ ፡ ገብቶኝ
እናገራለሁ ፡ አፌን ፡ ሞልቼ
??? ፡ በሮቼን
በምሥጋና(፫) ፡ ስሙን ፡ ላክብር ፡ እንደገና
በዕልልታ(፫) ፡ ዛሬም ፡ አለሁ ፡ በከፍታ
በምድረበዳው(፪)
ጥሎ ፡ የማይሄድ ፡ ጌታ ፡ የሚያሳርፍ ፡ ነው
ከእናቴ ፡ ማህጸን ፡ ስላወቀኝ ፡ ጌታ
እንዳልጠፋ ፡ እንዳልሞት ፡ በብዙ ፡ ጥበቃ
እየጠበቀኝ ፡ እየደገፈኝ
እረኛዬ ፡ ሆኖ ፡ ጌታ ፡ አሳደገኝ
መሪዬ ፡ ነህ ፡ ለእኔ ፡ ብልህ ፡ ምን ፡ ያንስሃል ፡ ኢየሱሴ
ውበት ፡ ደምግባቴ ፡ ብልህ ፡ ምን ፡ ያንስሃል ፡ ኢየሱሴ(፪)
|