ወዶ ፡ ዘማች (Wedo Zemach) - በረከት ፡ አለሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
በረከት ፡ አለሙ
(Bereket Alemu)

Bereket Alemu 1.jpg


(1)

ወዶ ፡ ዘማች
(Wedo Zemach)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፯ (2007)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 4:44
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የበረከት ፡ አለሙ ፡ አልበሞች
(Albums by Bereket Alemu)

ከተሸሸኩበት ፡ መንደሬ
መጣ ፡ ኢየሱስ ፡ ገባ ፡ ሰፈሬ
ጠራኝ ፡ ቀርቦ ፡ በቁልምጫው
ሊያስገባኝ ፡ ወደ ፡ ጉያው

   የወዳጄ ፡ የአምላኬ
   ጥሪው ፡ ደርሶኛል
   ምን ፡ አደርጋለሁ
   ቀሪው ፡ ዘመኔን ፡ ሰጥቼዋለሁ
   ይስራበት ፡ ይክበርበት
   ያለው ፡ አላማ ፡ ፈቃድ ፡ ሀሳቡ
   ይጠቅለል ፡ በእኔ ፡ ይድረስ ፡ ከግቡ

ሲጠራኝ (ክብር ፡ አይቶልኝ)
ሲለየኝ (ክብር ፡ አይቶልኝ)
ሲቀባኝ (ክብር ፡ አይቶልኝ)
ሲመርጠኝ (ክብር ፡ አይቶልኝ) (፪x)

   መገለጫው ፡ ነው ፡ መገለጫው
   ለሰማይ ፡ ወኪል ፡ የምድር ፡ ጨው
   የምድርን ፡ ክፋት
   መርገም ፡ ሰባሪ
   የሰላም ፡ ዘማች ፡ ለሰማይ ፡ ጥሪ (፪x)

ሲጠራኝ (ክብር ፡ አይቶልኝ)
ሲለየኝ (ክብር ፡ አይቶልኝ)
ሲቀባኝ (ክብር ፡ አይቶልኝ)
ሲመርጠኝ (ክብር ፡ አይቶልኝ (፪x)

   ማያንገራግረው ፡ ማያመቻምቸው
   ትዳር ፡ ባለበት ፡ ሰፈር
   ራሱን ፡ የማይጠምደው
   ጠሪውን ፡ ሲያስደስተው
   ሲገኝ ፡ በጸና ፡ እምነቱ
   ማረጉ ፡ ነው ፡ በላዩ
   ሚታየው ፡ ሽልማቱ (፪x)

ወዶ ፡ ዘማች ፡ ወዶ ፡ ዘማች
ለወንጌሉ ፡ ወዶ ፡ ዘማች
ፈቅዶ ፡ ዘማች ፡ ፈቅዶ ፡ ዘማች
ለዚህ ፡ ጥሪ ፡ ፈቅዶ ፡ ዘማች

   ማነው (ወዶ ፡ ዘማች)
   ማነው (ለዚህ ፡ ጥሪ)
   ማነው (ራሱን ፡ ሰቶ)
   ማነው (ጌታውን ፡ አስጠሪ)
   ማነው (እኔ ፡ ነኝ)
   ማነው (እኔ ፡ ነኝ)
   ማነው (እኔ ፡ ነኛ)
   ማነው (ለወንጌሉ)
   ማነው (ዘማች ፡ አርበኛ)

ማነው (፬x)
ማነው