ምሥጋናው ፡ ይታወጅ (Misganaw Yitawej) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Azeb Hailu 5.jpg


(5)

አልበም
(፭)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፱ (2017)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 4:23
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዜብ ፡ ኃይሉ ፡ አልበሞች
(Albums by Azeb Hailu)

ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ ማደሪያው
አለኝ ፡ ምሥጋና ፡ ይዤ ፡ የምገባው
ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ መቅደሱ
አለኝ ፡ አምልኮ ፡ የሚሆን ፡ ለእርሱ

ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ ማደሪያው
አለኝ ፡ ምሥጋና ፡ ይዤ ፡ የምገባው
ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ መቅደሱ
አለኝ ፡ አምልኮ ፡ የሚሆን ፡ ለእርሱ

በአደባባዩ ፡ በቤቱ ፡ ደጅ
ምሥጋናው ፡ ይታወጅ
በክብር ፡ ቤቱ ፡ ዙፋኑ ፡ ዙሪያ
ይዘመር ፡ ሃሌሉያ

በልቤ ፡ ሞልቶ ፡ የተረፈው
የምሥጋን ፡ ቃል ፡ ዝማሬ ፡ ነው
መክፈል ፡ ባልችልም ፡ የእርሱን ፡ ውለታ
ፊቱ ፡ ቀርቤ ፡ ላሰማ ፡ ዕልልታ
ላደረገልኝ ፡ ለሰራው ፡ ሁሉ
ወዳጅ ፡ ዘመዴ ፡ ክበር ፡ ይበሉ
በጸሎት ፡ ምልጃ ፡ ለቃተታችሁ
ዛሬ ፡ ምሥጋና፡ ቀን ፡ ነው ፡ አይዟችሁ

ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ ማደሪያው
አለኝ ፡ ምሥጋና ፡ ይዤ ፡ የምገባው
ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ መቅደሱ
አለኝ ፡ አምልኮ ፡ የሚሆን ፡ ለእርሱ

ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ ማደሪያው
አለኝ ፡ ምሥጋና ፡ ይዤ ፡ የምገባው
ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ መቅደሱ
አለኝ ፡ አምልኮ ፡ የሚሆን ፡ ለእርሱ

በአደባባዩ ፡ በቤቱ ፡ ደጅ
ምሥጋናው ፡ ይታወጅ
በክብር ፡ ቤቱ ፡ ዙፋኑ ፡ ዙሪያ
ይዘመር ፡ ሃሌሉያ

ስለቴን ፡ ልክፈል ፡ ቃል ፡ ኪዳኔን
ለክብርህ ፡ ቢሆን ፡ ብዬ ፡ ያልኩትን
ባይመጣጠን ፡ ከአንተ ፡ ውለታ
ግን ፡ ዝም ፡ አልልም ፡ ልሰዋው ፡ ላምጣ
ጣልቃ ፡ እየገባ ፡ በሕይወት ፡ መንገዴ
የመራኝ ፡ እጅህ ፡ ክንድህ ፡ አይደል ፡ እንዴ
ታዲያ ፡ ስለምን ፡ ዕልልታን ፡ ልርሳ
ይልቅ ፡ ልጨምር ፡ ላብዛ ፡ ሙገሳ ፡

ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ ማደሪያው
አለኝ ፡ ምሥጋና ፡ ይዤ ፡ የምገባው
ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ መቅደሱ
አለኝ ፡ አምልኮ ፡ የሚሆን ፡ ለእርሱ

ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ ማደሪያው
አለኝ ፡ ምሥጋና ፡ ይዤ ፡ የምገባው
ወደ ፡ አምላኬ ፡ ቤት ፡ ወደ ፡ መቅደሱ
አለኝ ፡ አምልኮ ፡ የሚሆን ፡ ለእርሱ

በአደባባዩ ፡ በቤቱ ፡ ደጅ
ምሥጋናው ፡ ይታወጅ
በክብር ፡ ቤቱ ፡ ዙፋኑ ፡ ዙሪያ
ይዘመር ፡ ሃሌሉያ