ምህረት ፡ ወረደ (Meheret Werede) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Tesfaye Chala 5.jpeg


(5)

ይታይ
(Yetay)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2011)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

 
"መምህር ፡ ሆይ ፡ ይህች ፡ ሴት ፡ ስታመነዝር ፡ ተገኝታ ፡ ተያዘች
ሙሴም ፡ እንደዚህ ፡ ያሉት ፡ እንዲወገሩ ፡ በህግ ፡ አዟል
አንተስ ፡ ስለእርሷ ፡ ምን ፡ ትላለህ"

ባያድላት ፡ እንጂ ፡ ቀኑ ፡ ቢከፋባት
እንደአንተዉ ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ ወግ ፡ ያናፈቃት
እንደአንቺው ፡ እንደእኔ ፡ ወግ ፡ እየናፈቃት
ተኳኩላ ፡ ወጣች ፡ ፀሐይ ፡ ስታልቅባት
ሳያት ፡ ሆዴ ፡ ባባ ፡ እንዴት ፡ ልታደጋት

ምነው ፡ እንደህልሟ ፡ በክብር ፡ በተዳረች
ለጠፊ ፡ ለአላፊ ፡ እንቃ??? ፡ አካሏን ፡ ሸጠች
ኀጢአት ፡ የሌለበት ፡ ይህ ፡ ሰው ፡ ይፍረድባት
እኔ ፡ ሲታየኝ ፡ ይህች ፡ ሴት ፡ ቀን ፡ አላት

ምህረት ፡ ወረደ ፡ ከላይ (ከላይ (፫x)) ፡ አዳኟ ፡ ይቅር ፡ አላት
ኀጢአት ፡ ያልተገኘበት ፡ ማን ፡ ይሆን ፡ ሚፈርድባት

ከእንግዲስ ፡ በቃው ፡ በለው ፡ አውጥቶ ፡ ሰው ፡ ለጣለው
ለተታለው ፡ ለዚያው ፡ ሰው ፡ እግዚአብሔር ፡ እቅድ ፡ አለው
ቆሻሻውን ፡ ይጠርግና ፡ እህህ ፡ ሸልሞ ፡ ያቆመዋል
ሰው ፡ አበቃ ፡ ባለ ፡ ቀን ፡ እግዚአብሔር ፡ ይጀምራል (፪x)

ዙሪያ ፡ ሲሰካ??? ፡ ቀን ፡ ሲጨላልም
አካሏን ፡ ሸጣ ፡ ውላ ፡ ብታድር
ለአፍታሪክ ፡ ??? ፡ ብቻ ፡ አትፈልግም
እንደሰው ፡ ሃሳብ ፡ እስቲ ፡ ዘመርላት???
ስም ፡ ተለጥፎባት ፡ ብትከሰስ
ሁሉን ፡ የሚያየው ፡ ዳኛ ፡ ጋር ፡ ስትደርስ
አትፍሪ ፡ ብሎ ፡ ምህረት ፡ ለገሳት
ሰው ፡ ያጨለመውን ፡ ቀን ፡ አወጣላት

(ያነሳል) ፡ ኀጢአተኛውን ፡ ሰው
(ያነሳል) ፡ ሸልሞ ፡ ሊያቆመው
(ያነሳል) ፡ ለክብሩ ፡ መግለጫ
(ያነሳል) ፡ ክብር ፡ እቃ ፡ ሊያደርገው
(ያነሳል) ፡ የቆሸሸውን ፡ ማንጻት
(ያነሳል) ፡ ማንጻት ፡ ነው ፡ ልማዱ
(ያነሳል) ፡ ቀን ፡ አለ ፡ ቀን ፡ አለው
(ያነሳል) ፡ በኀጢአት ፡ ለተጐዱ (፬x)