አፌ ፡ ሞላ (Afie Mola) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Tesfaye Chala 5.jpeg


(5)

ይታይ
(Yetay)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2011)
ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

 
የገባልኝ ፡ ኪዳን ፡ ልቤን ፡ እያስንሳው
ዘምር (፫x) ፡ እያለኝ (፪x)
ከተሰቀለበት ፡ በገናዬን ፡ ቃኘሁ
በአድደባባዮቹ ፡ እንዳምነው ፡ እንዳከብረው
ሞኝ ፡ ነው ፡ ጠላቴ ፡ ይህንን ፡ ዘነጋ
ጌታ ፡ ሳይለው ፡ ቀኔ ፡ እንደማይዘጋ

አዝ፦ አፌ ፡ ተሞላ ፡ በአዲስ ፡ ምሥጋና
ጥሩልኝ ፡ እስቲ ፡ ባለበገና
በቦታዬ ፡ ላይ ፡ ማህሌት ፡ እቆማለሁ
መቅደሱን ፡ በክብር ፡ አደንቀዋለሁ
ዘምር (፫x) ፡ ያለኝ ፡ ጌታ
የጠራኝ ፡ መረጠኝ ፡ የጠራኝ ፡ በደስታ
ዘምርልኝ ፣ ዘምር ፡ እንጂ ፣ ዘምር ፡ ያለኝ ፡ ጌታ
የጠራኝ ፡ መረጠኝ ፡ የጠራኝ ፡ በደስታ

በሞትና ፡ በእኔ ፡ መሃል ፡ አንድ ፡ እርምጃ ፡ ቀርቶ
በጭንቅ ፡ ቀን ፡ የሚረዳ ፡ የሚያግዝ ፡ ጠፍቶ
ዐይኖቼን ፡ ወደ ፡ ተራሮ ፡ እንኳን ፡ ባነሳ
እያሞካሸ ፡ የጠራኝ ፡ ወዳጄን ፡ ልረሳ

ቃሉን ፡ ልኮልኝ ፡ ከሰማይ ፡ ሃይሌን ፡ ያደሰው (ኦሆ)
ውበት ፡ የሰጠው ፡ እርሱ ፡ ነው ፡ ለፈራረሰው (ኦሆ)
የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ ነው ፡ የእኔ ፡ መኖሪያ (አሃ)
ልዘምር ፡ ሳላናጋግር ፡ ሳልሰማ ፡ ዙሪያ (ኦሆ)

አዝ፦ አፌ ፡ ተሞላ ፡ በአዲስ ፡ ምሥጋና
ጥሩልኝ ፡ እስቲ ፡ ባለበገና
በቦታዬ ፡ ላይ ፡ ማህሌት ፡ እቆማለሁ
መቅደሱን ፡ በክብር ፡ አደንቀዋለሁ
ዘምር (፫x) ፡ ያለኝ ፡ ጌታ
የጠራኝ ፡ መረጠኝ ፡ የጠራኝ ፡ በደስታ
ዘምርልኝ ፣ ዘምር ፡ እንጂ ፣ ዘምር ፡ ያለኝ ፡ ጌታ
የጠራኝ ፡ መረጠኝ ፡ የጠራኝ ፡ በደስታ

የገባልኝ ፡ ኪዳን ፡ ልቤን ፡ እያስንሳው
ዘምር (፫x) ፡ እያለኝ
ዘምርልኝ ፣ ዘምር ፡ እንጂ ፣ ዘምር ፡ እያለኝ
ቃል ፡ አለኝ ፡ ከሰማይ ፡ ኪዳን ፡ ከአምላኬ ፡ ጋር
ተስፋዬን ፡ አስቦ ፡ ሁሌ ፡ ልቤ ፡ ተረጋጋ
ሃሳቡ ፡ ሳይሞላ ፡ ጠላቴ ፡ ሲሸበር
ምሥጋና ፡ እና ፡ አምልኮ ፡ ይኸው ፡ በእኔ ፡ ሰፈር

አዝ፦ አፌ ፡ ተሞላ ፡ በአዲስ ፡ ምሥጋና
ጥሩልኝ ፡ እስቲ ፡ ባለበገና
በቦታዬ ፡ ላይ ፡ ማለት ፡ እቆማለሁ
መቅደሱን ፡ በክብር ፡ አደንቀዋለሁ
ዘምር (፫x) ፡ ያለኝ ፡ ጌታ
የጠራኝ ፡ መረጠኝ ፡ የጠራኝ ፡ በደስታ
ዘምርልኝ ፣ ዘምር ፡ እንጂ ፣ ዘምር ፡ ያለኝ ፡ ጌታ
የጠራኝ ፡ መረጠኝ ፡ የጠራኝ ፡ በደስታ
ዘምር (፫x) ፡ እያለኝ
የጠራኝ ፡ መረጠኝ ፡ የጠራኝ ፡ በደስታ