በማዕበሉ ፡ ላይ (Bemaebelu Lay) - ተስፋዬ ፡ ጫላ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጫላ
(Tesfaye Chala)

Tesfaye Chala 4.jpg


(4)

የበላይ ፡ ነህ ፡ ጌታ
(Yebelay Neh Gieta)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 4:21
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጫላ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Chala)

አዝ:- በማዕበሉ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ
በወጀቡ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ነህ (፬x)

ያላሰብኩት ፡ ቢሆን ፡ አሃሃሃ ፡ ነገር ፡ ቢቀያየር ፡ ኦሆሆሆ
ተስፋ ፡ ያደረኩት ፡ አሃሃሃ ፡ ሸንበቆው ፡ ቢሰበር ፡ ኦሆሆሆ
ዐይን ፡ የሚጣልበት ፡ አሃሃሃ ፡ አንድ ፡ እንኳን ፡ ቢጠፋ ፡ ኦሆሆሆ
ወጀቡ ፡ በርትቶ ፡ አሃሃሃ ፡ ለነገ ፡ ቢከፋ ፡ ኦሆሆሆ

ድምጹን ፡ ሳልሰማ ፡ የማዕበሉን
ሳላይ ፡ ያን ፡ ሃይል ፡ የንፋሱን
በሙሉ ፡ ልቤ ፡ ጠራሃለው
ለአንተ ፡ የማይሰግድ ፡ የማይቆም ፡ ማነው

አዝ:- በማዕበሉ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ
በወጀቡ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ነህ (፪x)

ቀይ ፡ ባሕር ፡ ከፊቴ ፡ አሃሃሃ ፡ ቆሞ ፡ ሲያስጨንቅኝ ፡ ኦሆሆሆ
ፈርንም ፡ ከሁአላ ፡ አሃሃሃ ፡ ሊመጣ ፡ ቢውጠኝ ፡ ኦሆሆሆ
የማመልክህ ፡ አምላክ ፡ አሃሃሃ ፡ ወዴት ፡ ነህ ፡ እላለሁ ፡ ኦሆሆሆ
በቃልህ ፡ እኔ ፡ ቆሜ ፡ አሃሃሃ ፡ ስምህን ፡ እጠራዋለሁ ፡ ኦሆሆሆ

ጩኀቴን ፡ ሰምተህ ፡ ከሰማያት
እራርተህልኝ ፡ እንደአባት
መንጥቀህ ፡ ስንቴ ፡ አውጥተኀኛል
የአምናው ፡ ለነገ ፡ እምነት ፡ ሆኖኛል

አዝ:- በማዕበሉ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ
በወጀቡ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ነህ (፬x)