Tesfaye Chala/Bamare Qenie/Bamare Qenie

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጫላ ርዕስ ባማረ ቅኔ

አዝ ባማረ ቅኔ ለኢየሱስ ምሥጋና ቃሉን የሚያደርግ ድንቅ አምላክ ነውና ደመናም ባላይ ሸለቆው ይሞላል ሰው የማይችለው ለእግዚአብሔር ይቻላል

እኔስ ተስፋ አልቆርጥም ፍፁም አላፍርም ባዳነኝ ጌታ አይቻለሁና በዐይኔ ያስጨነቀኝን ሲመታ ነገር ባይሞላ ባይሳካ ኢየሱስ ምን ይሳነዋል ከሞተው አንበሳ ሆድ ውስጥ ጣፋጭ ጣፋጭ ማር ያወጣል (፪x)

አዝ ባማረ ቅኔ ለኢየሱስ ምሥጋና ቃሉን የሚያደርግ ድንቅ አምላክ ነውና ደመናም ባላይ ሸለቆው ይሞላል ሰው የማይችለው ለእግዚአብሔር ይቻላል

ለምን ልጐሳቆል ልዘን ለምንስ ልቆዝም በእንባ ተዓምር ያስለመደኝ አምላክ መቼ ክንዱ ደከመና በታሰርኩበት ወህኒ ውስጥ ሆ እያልኩኝ እዘምራለሁ የጠላቶቼን ደጅ በእምነት በዝማሬ አፈርሳለሁ (፪x)

አዝ ባማረ ቅኔ ለኢየሱስ ምሥጋና ቃሉን የሚያደርግ ድንቅ አምላክ ነውና ደመናም ባላይ ሸለቆው ይሞላል ሰው የማይችለው ለእግዚአብሔር ይቻላል

ውድቀቴን ጠላቴ ሰምቶ ከበሮ ተይዞ ሲጨፈር አምላኩ ጥሎታል ዛሬስ ተብሎ አዋጅ ሲነገር ሰው የማይጥል ጌታ አምላኬ ኃያል ክንዱን ሲዘረጋ ጠላቶቼ ሁሉ አለቁ በአንዲት የአህያ መንጋጋ (፪x)

አዝ ባማረ ቅኔ ለኢየሱስ ምሥጋና ቃሉን የሚያደርግ ድንቅ አምላክ ነውና ደመናም ባላይ ሸለቆው ይሞላል ሰው የማይችለው ለእግዚአብሔር ይቻላል

ሰላሙን ሞልቶ አባቴ በመስቀሉ ስራ አሳረፈኝ ወደ ክብሩ ልጁም መንግሥት በታላቅ ፍቅሩ አፈለሰኝ ልጁን ለእኔ የሰጠ አምላክ ሌላ ምን ምን ይሳነዋል ባዶ ሸለቆዬ ሞልቶ ተርፎ ለአገር ሁሉ ይፈሳል (፪x)

አዝ ባማረ ቅኔ ለኢየሱስ ምሥጋና ቃሉን የሚያደርግ ድንቅ አምላክ ነውና ደመናም ባላይ ሸለቆው ይሞላል ሰው የማይችለው ለእግዚአብሔር ይቻላል