Solomon Yirga/Meazayie Neh/Ende Balehamsa Qen

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

| ርዕስ = እንደ ፡ ባለሃምሳ ፡ ቀን | Title = Ende BaleHamsa Qen | ዘማሪ = ሰለሞን ፡ ይርጋ | Artist = Solomon Yirga | Volume = 2 | አልበም = መዓዛዬ ፡ ነህ | Album = Meazayie Neh | Track = 6 | Year = ፳ ፻ ፫ (2011)

ኧረ ፡ ምን ፡ ይባል ፡ ምን ፡ ይባል ፡ ይህ ፡ ጌታ

እኔ ፡ ምለው ፡ አጣሁ ፡ አስገረመኝ ፡ ጌታ

ምነው ፡ ሌላ ፡ ነገር ፡ ሌላ ፡ ነገር ፡ ባይኖር

ቀንና ፡ ሌሊቱን ፡ እልል ፡ ሲባል ፡ ሲመለክ ፡ ቢታደር

በህልውናው ፡ ውስጥ ፡ እልም ፡ ጥፍት ፡ ስምጥ ፡ ብሎ ፡ ማደር


አዝ፦ እንደ ፡ ባለሃምሳ ፡ ቀን ፡ እንደ ፡ መጀመሪያው

ና ፡ ደግመህ ፡ በሕይወቴ

ና ፡ ደግመህ ፡ በሕይወቴ ፡ ሙላኝ ፡ በመንፈስህ

ልሂድ ፡ ወደሰማይ ፣ ልሂድ ፡ ወደሰማይ (፪x)


ከአቻምናው ፡ የአምናው ፡ የዘንድሮው ፡ ባሰ

በተጠጋሁት ፡ ቁጥር ፡ ሕይወቴ ፡ እየራሰ ፡ እየረሰረሰ

ህልውናውን ፡ ወደድኩ ፡ ከሁሉ ፡ የበለጠ

መገኘቱን ፡ ናፈቅሁ ፡ ከሁሉ ፡ የበለጠ

ኢየሱሴን ፡ ወደድኩ ፡ ከሁሉ ፡ የበለጠ

ኢየሱሴን ፡ ናፈቅሁ ፡ ከሁሉ ፡ የበለጠ


አዝ:- እንደ ፡ ባለሃምሳ ፡ ቀን ፡ እንደ ፡ መጀመሪያው

ና ፡ ደግመህ ፡ በሕይወቴ

ና ፡ ደግመህ ፡ በሕይወቴ ፡ ሙላኝ ፡ በመንፈስህ

ልሂድ ፡ ወደሰማይ ፣ ልሂድ ፡ ወደሰማይ (፪x)


ሁልጊዜ ፡ አዲስ ፡ ነገር ፡ አዲስ ፡ ነገር ፡ አለህ

ቢቀዳ ፡ ቢቀዳ ፡ እንደማያልቅ ፡ እንደመልካም ፡ ምንጭ ፡ ነህ

ምን ፡ ብዬ ፡ ልግለጽህ (የእኔ ፡ ጌታ) ምን ፡ ብዬ ፡ ልናገር

እጅጉን ፡ ድንቅ ፡ ነህ (፪x)


ዋላ ፡ የውኃ ፡ ምንጭ ፡ ሁሌ ፡ እንደምትናፍቅ (፪x)

ነፍሴ ፡ አንተን ፡ ተጠማች ፡ አንተን ፡ ፈለገችህ (፪x)

ማለዳ ፡ ተነስታ ፡ ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ (፪x) ፡ ኢየሱስ ፡ አለችህ