Sofia Shibabaw/Sema Belew/Menem Behon

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ


የኔን ፡ ጠያፉን ፡ ሕይወት
ውበትን ፡ ጨምሮበት
ሳላውቅ ፡ ባለማመን ፡ ስላደረኩት

አገኘሁ ፡ ምህረት (፪x)

ምንም ፡ ብሆን ፡ ጌታ ፡ ጌታዬ ምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ቃሉ አሳምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ደሙ ፡ አሳምሮኝ
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል
ከሰይጣን ፡ አፍ ፡ አውጥቶኛል
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል

ከጉድ ፡ ከእፍረት ፡ አውጥቶኛል

በምህረቱ ፡ ባለጠጋ
ኢየሱስ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ተጠጋ
ምንም ፡ ብሆን ፣ ምንም ፡ ብሆን

አልጣለኝም ፡ ጌታ ፡ አለሁ ፡ በእርሱ ፡ ጎን (፪x)

ከቤቴ ፡ እንዳትገባ ፡ ብዬው ፡ የነበረው
በፍቅር ፡ መጣና ፡ ታሪኬን ፡ ቀየረው
አንድ ፡ ሁሉት ፡ ብሎ ፡ የሚቆጠር ፡ ጽድቄ
ምን ፡ ነበረኝና ፡ ከአብ ፡ፊት: ርቄ
በመካከል ፡ ገብቶ ፡ ጠበቃዬ ፡ ዋሴ

ደጉ ፡ ኢየሱሴ

ግርማን ፡ ከሚያሳጣኝ ፡ ሥራዬ ፡ ተሽሮ
ዛሬስ ፡ እገኛለሁ ፡ ቆሻሻዬን ፡ ሁሉ
ደሙ ፡ አሳምሮ
ቃሉ ፡ አሳምሮ

መንፈሱ ፡ አሳምሮ

ምንም ፡ ብሆን ፡ ጌታዬ ምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ቃሉ አሳምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ደሙ ፡ አሳምሮኝ
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል
ከሰይጣን ፡ አፍ ፡ አውጥቶኛል
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል

ከጉድ ፡ ከእፍረት ፡ አውጥቶኛል


በምህረቱ ፡ ባለጠጋ
ኢየሱስ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ተጠጋ
ምንም ፡ ብሆን ፣ ምንም ፡ ብሆን

አልጣለኝም ፡ ጌታ ፡ አለሁ ፡ በእርሱ ፡ ብሆን (፪x)

የት ፡ አለኝ ፡ በጐነት ፡ የለኝ ፡ መልካምነት
ልናገር ፡ በድፍረት ፡ እንዲህ ፡ ነው ፡ ምልበት
የተላለፈብኝ ፡ የመርገም ፡ ሀረጌ
አየሁት ፡ በክንዱ ፡ ሲሰብረው ፡ ጌታዬ
እኔነቴን ፡ አልፎ ፡ ለመጣው ፡ ሊፍክር

ኧረ ፡ እንዴት ፡ አልዘምር

ምንም ፡ ብሆን ፡ ይህን ፡ አረገልኝ ፡ ጌታ
እስቲ ፡ ላመስግነው ፡ ከውስጥ ፡ ከመንፈሴ
ተሰብሯል ፡ ቀምበሬ
የድል ፡ ቀን ፡ ነው ፡ ዛሬ

ያክብረው ፡ ከንፈሬ

ምንም ፡ ብሆን ፡ ጌታዬ ምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ቃሉ አሳምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ደሙ ፡ አሳምሮኝ
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል
ከሰይጣን ፡ አፍ ፡ አውጥቶኛል
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል

ከጉድ ፡ ከእፍረት ፡ አውጥቶኛል

በምህረቱ ፡ ባለጠጋ
ኢየሱስ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ተጠጋ
ምንም ፡ ብሆን ፣ ምንም ፡ ብሆን

አልጣለኝም ፡ ጌታ ፡ አለሁ ፡ በእርሱ ፡ ብሆን (፪x)

በቃ ፡ ልጅ ፡ ነኝ ፡ እኔ
ተሰብሯል ፡ ኩነኔ
ተጥሏል ፡ ከሳሼ

ማጥ ፡ ውስጥ ፡ አልገኝም ፡ ዳግም ፡ ተመልሼ

በምህረቱ ፡ ባለጠጋ
ኢየሱስ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ተጠጋ
ምንም ፡ ብሆን ፣ ምንም ፡ ብሆን

አልጣለኝም ፡ ጌታ ፡ አለሁ ፡ በእርሱ ፡ ብሆን (፪x) </poem> }}