የማመልከው (Yemamelkew) - ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል
(Samuel Tesfamichael)

Samuel Tesfamichael 3.jpg


(3)

ምሳሌ ፡ የሌለህ
(Misale Yeleleh)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2012)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሳሙኤል ፡ ተስፋሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Samuel Tesfamichael)

አባቶች ፡ በእምነት ፡ አምልከውት ፡ አለፉ
ነቢያት ፡ አወሩለት ፡ መለከትን ፡ ነፉ
ሓዋሪያት ፡ የሰሙት ፡ በዐይናቸው ፡ ያዩት
በእጆቻችሀው ፡ ዳሰው ፡ የመሰከሩለት
መቃብር ፡ ፈንቅሎ ፡ ሞትን ፡ ድል ፡ የነሳው
እርሱን ፡ በማምለኬ ፡ እኔ ፡ እንጓደዳለሁ

ከሰማያት ፡ በላይ ፡ ከፍ ፡ ብሎ ፡ ያለ
በዘምናት ፡ መሃል ፡ እጅግ ፡ የከበረ
በሃይል ፡ በችሎቱ ፡ ዝናው ፡ የገነነ
በፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ ላይ ፡ የተመሰገነ
ይሄ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ይሄ ፡ ነው
ይሄ ፡ ነው ፡ አምላክ ፡ ይሄ ፡ ነው (፪x)
እኔ ፡ የማመልከው

አዝ፦ የማመልከው ፡ ይህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
የማደንቀው ፡ የምሰግድለት
እርሱ ፡ ብቻ ፡ የአማልክት ፡ አምላክ
የማመልከው ፡ ይህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
የማደንቀው ፡ የምሰግድለት
እግዚአብሔር ፡ የአማልክት ፡ አምላክ

ፀሐይን ፡ አቁሞ ፡ ጨረቃን ፡ ያዘገየ
አሰራሩ ፡ ልዩ ፡ ከሁሉ ፡ የተለየ
ባሕርን ፡ እንደግድግዳ ፡ እንደክምር ፡ ያደረገው
የጥንቱ ፡ እግዚአብሔር ፡ ዛሬም ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው
ይሄ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ይሄ ፡ ነው
አምላክስ ፡ ካሉ ፡ እንዲህ ፡ ነው
መኖር ፡ ካልቀረ ፡ እርሱ ፡ ነው
ካመለኩ ፡ አይቀር ፡ እርሱን ፡ ነው

አዝ፦ የማመልከው ፡ ይህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
የማደንቀው ፡ የምሰግድለት
እርሱ ፡ ብቻ ፡ የአማልክት ፡ አምላክ (፪x)

የአህዛብ ፡ አማልክት ፡ ጣኦታቶች ፡ ናቸው
አይሰሙ ፡ አያዩ ፡ ቢጠሩ ፡ አይሰሟቸው
አምላካቸው ፡ ይቀስቀስ ፡ ተኝቷል ፡ ወይ ፡ ሲባል
እኔ ፡ የማመልከው ፡ በእሳት ፡ ይመልሳል
የተነሱበትን ፡ ሁሉ ፡ ያደቀቀ
በአሸናፊነቱ ፡ ግድሉ ፡ የታወቀ
ይሄ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ይሄ ፡ ነው
አምላክስ ፡ ካሉ ፡ እንዲህ ፡ ነው
መኖር ፡ ካልቀረ ፡ እርሱ ፡ ነው
ካመለኩ ፡ አይቀር ፡ እርሱን ፡ ነው

አዝ፦ የማመልከው ፡ ይህ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
የማደንቀው ፡ የምሰግድለት
እርሱ ፡ ብቻ ፡ የአማልክት ፡ አምላክ (፪x)