ወረት ፡ አያውቀው ፡ ጌታዬ (Weret Ayawqew Gietayie)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ


አዝ፦ ወረት ፡ አያውቀው ፡ ጌታዬ
ዘለዓለም ፡ ምስጢረኛዬ
የልቤን ፡ አጫውተዋለሁ
ገበናዬን ፡ አሳየዋለሁ (፪x)

ለሰው ፡ ብመስል ፡ የደላው
ውስጤ ፡ ግን ፡ እሳት ፡ ንዳድ ፡ ነው
አፌን ፡ አልከፍትም ፡ ለማንም
ጌታ ፡ ያውቃል ፡ ትርፌን ፡ ጉድለቴንም (፪x)

አዝ፦ ወረት ፡ አያውቀው ፡ ጌታዬ
ዘለዓለም ፡ ምስጢረኛዬ
የልቤን ፡ አጫውተዋለሁ
ገበናዬን ፡ አሳየዋለሁ (፪x)

ድብቅ ፡ አድርጌ ፡ ምስጢሬን
አስጸያፊውን ፡ ስራዬን
እነግረዋለሁኝ ፡ ታማኝ ፡ ነው
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ጊዜ ፡ የማይለውጠው (፪x)

አዝ፦ ወረት ፡ አያውቀው ፡ ጌታዬ
ዘለዓለም ፡ ምስጢረኛዬ
የልቤን ፡ አጫውተዋለሁ
ገበናዬን ፡ አሳየዋለሁ (፪x)

ሳዝን ፡ ስተክዝ ፡ በኑሮ
እሰማለሁ ፡ እሮሮ
ብቸኝነት ፡ ሲያጠቃቃኝ
በኢየሱስ ፡ መጽናናት ፡ አለኝ (፪x)

አዝ፦ ወረት ፡ አያውቀው ፡ ጌታዬ
ዘለዓለም ፡ ምስጢረኛዬ
የልቤን ፡ አጫውተዋለሁ
ገበናዬን ፡ አሳየዋለሁ (፪x)

አላምናቸው ፡ ወዳጆቼን
ፏደኞቼን ፡ ዘመዶቼን
ያጋልጡኛል ፡ ጠብቀው
አይችሉትም ፡ ጉዴን ፡ ተሸክመው (፪x)

አዝ፦ ወረት ፡ አያውቀው ፡ ጌታዬ
ዘለዓለም ፡ ምስጢረኛዬ
የልቤን ፡ አጫውተዋለሁ
ገበናዬን ፡ አሳየዋለሁ (፪x)