ታጋሽና ፡ ሩህሩህ ፡ አምላክ (Tagashena Ruhruh Amlak)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

የስቱን ፡ ጸባይ ፡ ነው ፡ አንተ ፡ እኮ ፡ የቻልከው
እያባበልክ ፡ ይዘህ ፡ አንተ ፡ የምታኖረው
እውነትም ፡ ፍቅር ፡ ነህ ፡ ሌላ ፡ ማንም ፡ የለም
ደከመኝ ፡ ሰለቸኝ ፡ መረረኝ ፡ አትልም

አዝ፦ ታጋሽና ፡ ሩህሩህ ፡ አምላክ ፡ አንተ ፡ ነህ
እስከ ፡ ሺ ፡ ትውልድ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህ
አንዴና ፡ ሁለቴ ፡ አይተህ ፡ አትሰለችም
እንደየአመሉ ፡ ታቅፋለህ ፡ ሁሉንም

ሰው ፡ የሰለችንን ፡ ከአፉ ፡ የተፋንን
እግዚአብሔር ፡ ግን ፡ ወዶ ፡ የሚያኖረን ፡ ስንቶች ፡ ነን
መልካም ፡ ሆነን ፡ አይደል ፡ የምንኖር ፡ በቤቱ
ስለበዛለን ፡ ነው ፡ የጌታ ፡ ምህረቱ

አዝ፦ ታጋሽና ፡ ሩህሩህ ፡ አምላክ ፡ አንተ ፡ ነህ
እስከ ፡ ሺ ፡ ትውልድ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህ
አንዴና ፡ ሁለቴ ፡ አይተህ ፡ አትሰለችም
እንደየአመሉ ፡ ታቅፋለህ ፡ ሁሉንም

አመሌ ፡ ጠማማ ፡ ከሰው ፡ የማይገጥም
በቀኝ ፡ ሲሉኝ ፡ ግራ ፡ ፍፁም ፡ አልመችም
አንተ ፡ ግን ፡ አጸለች ፡ እውነትም ፡ ፍቅር ፡ ነህ
ሁሌ ፡ በፈገግታ ፡ ትቀበለኛለህ

አዝ፦ ታጋሽና ፡ ሩህሩህ ፡ አምላክ ፡ አንተ ፡ ነህ
እስከ ፡ ሺ ፡ ትውልድ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህ
አንዴና ፡ ሁለቴ ፡ አይተህ ፡ አትሰለችም
እንደየአመሉ ፡ ታቅፋለህ ፡ ሁሉንም

የሰው ፡ ልብ ፡ ከሁሉ ፡ ይልቅ ፡ ተንኮለኛ
እጅግም ፡ ከፉ ፡ ነው ፡ መስሎ ፡ አመለኛ
ቢሆንም ፡ አትሰለች ፡ ተሸክመኸዋል
እግዚአብሔር ፡ ፍቅር ፡ ነህ ፡ ክብር ፡ ይገባሃል

አዝ፦ ታጋሽና ፡ ሩህሩህ ፡ አምላክ ፡ አንተ ፡ ነህ
እስከ ፡ ሺ ፡ ትውልድ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህ
አንዴና ፡ ሁለቴ ፡ አይተህ ፡ አትሰለችም
እንደየአመሉ ፡ ታቅፋለህ ፡ ሁሉንም