ኦ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ሥራህ ፡ ድንቅ ፡ ነው (O Gieta Hoy Serah Denq New)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ ኦ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ሥራህ ፡ ድንቅ ፡ ነው (፫x)
አደራረግህ ፡ ከሰው ፡ ልዩ ፡ ነው
እጅግ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሆይ
ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው

1. ሰው ፡ በቃ ፡ ብሎ ፡ የገነዘውን
ድንጋይ ፡ አትሞ ፡ የቀበረውን
መቃብር ፡ ከፍተህ ፡ ድንጋይ ፡ ፈነቀልህ
መግነዘን ፡ ፈተህ ፡ በነጻ ፡ ለቀህ
በሕይወት ፡ ታኖራለህ

አዝ፦ ኦ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ሥራህ ፡ ድንቅ ፡ ነው (፫x)
አደራረግህ ፡ ከሰው ፡ ልዩ ፡ ነው
እጅግ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሆይ
ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው

2. አሥራ ፡ ሁለት ፡ ዓመት ፡ ደሜ ፡ እጅግ ፡ ፈሷል
ሐብቴም ፡ ንብረቴም ፡ በከንቱ ፡ አልቋል
ተስፋ ፡ የለህሽም ፡ በቃ ፡ ያሉኝ
ጌታዬን ፡ ዳስሼ ፡ ፈውስ ፡ አገኘሁኝ
ተመስገን ፡ አልኩኝ

አዝ፦ ኦ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ሥራህ ፡ ድንቅ ፡ ነው (፫x)
አደራረግህ ፡ ከሰው ፡ ልዩ ፡ ነው
እጅግ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሆይ
ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው

3. ተስፋ ፡ ተቆርጦ ፡ ምን ፡ ይሁን ፡ ሲባል
እምነት ፡ ሲጠፋ ፡ ጉልበትም ፡ ሲዝል
በተዘጋ ፡ በር ፡ በድንገት ፡ ገብተህ
በሚያበራ ፡ ልብስ ፡ በክብር ፡ ተገልጠህ
ታሳርፋለህ

አዝ፦ ኦ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ሥራህ ፡ ድንቅ ፡ ነው (፫x)
አደራረግህ ፡ ከሰው ፡ ልዩ ፡ ነው
እጅግ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሆይ
ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው

4. ብዙዎች ፡ እያሉ ፡ የተከበሩ
በዕውቀት ፡ ያጌጡ ፡ በወርቅ ፡ በብሩ
እንደ ፡ እኔ ፡ ያለ ፡ ደካማን ፡ መርጠህ
ብርቱን ፡ አሳፈርክ ፡ ስምህን ፡ አክብረህ
አንተ ፡ ድንቅ ፡ ነህ

አዝ፦ ኦ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ሥራህ ፡ ድንቅ ፡ ነው (፫x)
አደራረግህ ፡ ከሰው ፡ ልዩ ፡ ነው
እጅግ ፡ ልዩ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሆይ
ከአእምሮ ፡ በላይ ፡ ነው